በጎነት የህሊና እርካታ ይሰጣል – በጎ አድራጊ ወጣቶች
ሀዋሳ: ጳጉሜ 03/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጎ ማድረግ የህሊና እርካታ የሚሰጥ በመሆኑ ሰዎች ለበጎ ሥራ ሊነሳሱ እንደሚገባ በቡታጅራ ከተማ በጎ አድራጊ ወጣቶች ተናግረዋል::
በቡታጅራ ከተማ ጳጉሜ 03 ቀን 2015 ዓ.ም የበጎነት ቀን በሚል በተለያዩ በጎ ተግባራት ተከብሮ ውሏል::
የከተማ ፅዳት ሥራ ሲያከናውኑ ያገኘናቸው የከተማዋ ወጣቶች መልካም ማድረግ እና በጎ ተግባር መፈፀም ካሳደጉን ወላጆቻችን የተማርነው ነገር ነው ብለዋል::
ይህ በጎ ሥራ በምንም ሊተካ የማይችልና የመንፈስ እርካታ የሚያስገኝ መሆኑን ገልጸዋል::
ዛሬ በመላ ኢትዮጵያ በሚከበረው የበጎነት ቀን ላይ ይህን ተግባር መፈፀም በመቻላችን ደስተኞች ነን ሲሉ ተናግረዋል::
ሌሎችም ወጣቶች መሠል ተግባራትን በማድረግ ለራሳቸውም ሆነ ለሌላ ሠው የደስታ ምንጭ መሆን እንደሚችሉ ጠቁመዋል::
የቡታጅራ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አማን በድሩ በበጎነት ቀን የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል::
የከተማ ፅዳት፣ የአልባሳት ድጋፍ፣ የደብተር ድጋፍና የእስክርቢቶ ድጋፍ እንዲሁም የአረጋዊያን ቤቶችን የማደስና ማዕድ የማጋራት ሥራ የመርሀግብሩ አካል ናቸው ብለዋል::
በተለይ ወጣቱ ለበጎ ሥራ እያሳየ ያለው ተነሳሽነት የሚደነቅ ነው ያሉት ምክትል ሃላፊው ላከናወኑት መልካም ተግባርም ምስጋና አቅርበዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ

More Stories
በሀሬ ተፋሰስበ በ27 ቀናት ወስጥ 35 ሄክታር መሬት ላይ እርከን ፣ አፈር እቀባና የተለያዩ ዕፅዋት ተከላ መከናወኑ ተገለፀ
አዲሱ የቦንጋ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን የኡፋ እና የውሽውሽ ከተሞችን ያካተተ መሆኑን በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት ዲን አቶ ደጉ በቀለ ገለጹ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን በየዓመቱ ህዳር 29 ቀን እንዲከበር ሲወሰን ዓላማው ብሔር ብሔረሰቦች ባህሎቻቸውን በመለዋወጥ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር ሃገራዊ መግባባትን እንዲፈጥሩ ማድረግ ነው – የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር