በጎነት የህሊና እርካታ ይሰጣል – በጎ አድራጊ ወጣቶች
ሀዋሳ: ጳጉሜ 03/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጎ ማድረግ የህሊና እርካታ የሚሰጥ በመሆኑ ሰዎች ለበጎ ሥራ ሊነሳሱ እንደሚገባ በቡታጅራ ከተማ በጎ አድራጊ ወጣቶች ተናግረዋል::
በቡታጅራ ከተማ ጳጉሜ 03 ቀን 2015 ዓ.ም የበጎነት ቀን በሚል በተለያዩ በጎ ተግባራት ተከብሮ ውሏል::
የከተማ ፅዳት ሥራ ሲያከናውኑ ያገኘናቸው የከተማዋ ወጣቶች መልካም ማድረግ እና በጎ ተግባር መፈፀም ካሳደጉን ወላጆቻችን የተማርነው ነገር ነው ብለዋል::
ይህ በጎ ሥራ በምንም ሊተካ የማይችልና የመንፈስ እርካታ የሚያስገኝ መሆኑን ገልጸዋል::
ዛሬ በመላ ኢትዮጵያ በሚከበረው የበጎነት ቀን ላይ ይህን ተግባር መፈፀም በመቻላችን ደስተኞች ነን ሲሉ ተናግረዋል::
ሌሎችም ወጣቶች መሠል ተግባራትን በማድረግ ለራሳቸውም ሆነ ለሌላ ሠው የደስታ ምንጭ መሆን እንደሚችሉ ጠቁመዋል::
የቡታጅራ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አማን በድሩ በበጎነት ቀን የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል::
የከተማ ፅዳት፣ የአልባሳት ድጋፍ፣ የደብተር ድጋፍና የእስክርቢቶ ድጋፍ እንዲሁም የአረጋዊያን ቤቶችን የማደስና ማዕድ የማጋራት ሥራ የመርሀግብሩ አካል ናቸው ብለዋል::
በተለይ ወጣቱ ለበጎ ሥራ እያሳየ ያለው ተነሳሽነት የሚደነቅ ነው ያሉት ምክትል ሃላፊው ላከናወኑት መልካም ተግባርም ምስጋና አቅርበዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ
More Stories
ቆሻሻን በአግባቡ በማስወገድ ከተማዋ ፅዱና ውብ እንድትሆን የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ነው – የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቋሚነት የሚደገፉበት ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የቡርጂ ዞን አስተዳደር አስታወቀ
“አንድ ሰው ወደዚህች ምድር ሲመጣ እንዲሰራ የተፈቀደለትና የሚጠበቅበት ነገር አለ” – ታደሰ ገብሬ /ጃክሰን/