በጎነት የህሊና እርካታ ይሰጣል – በጎ አድራጊ ወጣቶች
ሀዋሳ: ጳጉሜ 03/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጎ ማድረግ የህሊና እርካታ የሚሰጥ በመሆኑ ሰዎች ለበጎ ሥራ ሊነሳሱ እንደሚገባ በቡታጅራ ከተማ በጎ አድራጊ ወጣቶች ተናግረዋል::
በቡታጅራ ከተማ ጳጉሜ 03 ቀን 2015 ዓ.ም የበጎነት ቀን በሚል በተለያዩ በጎ ተግባራት ተከብሮ ውሏል::
የከተማ ፅዳት ሥራ ሲያከናውኑ ያገኘናቸው የከተማዋ ወጣቶች መልካም ማድረግ እና በጎ ተግባር መፈፀም ካሳደጉን ወላጆቻችን የተማርነው ነገር ነው ብለዋል::
ይህ በጎ ሥራ በምንም ሊተካ የማይችልና የመንፈስ እርካታ የሚያስገኝ መሆኑን ገልጸዋል::
ዛሬ በመላ ኢትዮጵያ በሚከበረው የበጎነት ቀን ላይ ይህን ተግባር መፈፀም በመቻላችን ደስተኞች ነን ሲሉ ተናግረዋል::
ሌሎችም ወጣቶች መሠል ተግባራትን በማድረግ ለራሳቸውም ሆነ ለሌላ ሠው የደስታ ምንጭ መሆን እንደሚችሉ ጠቁመዋል::
የቡታጅራ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አማን በድሩ በበጎነት ቀን የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል::
የከተማ ፅዳት፣ የአልባሳት ድጋፍ፣ የደብተር ድጋፍና የእስክርቢቶ ድጋፍ እንዲሁም የአረጋዊያን ቤቶችን የማደስና ማዕድ የማጋራት ሥራ የመርሀግብሩ አካል ናቸው ብለዋል::
በተለይ ወጣቱ ለበጎ ሥራ እያሳየ ያለው ተነሳሽነት የሚደነቅ ነው ያሉት ምክትል ሃላፊው ላከናወኑት መልካም ተግባርም ምስጋና አቅርበዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ

More Stories
የመምህርነት ሙያ ትውልድን የመቅረፅና ሀገርን የማነፅ ታላቅ የስልጣኔና ማህበራዊ የዜግነት ኃላፊነት በመሆኑ ተመራቂዎች ራሳቸውን ለማብቃት መትጋት አለባቸው – ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ
የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በተሻሻለ የስልጠና ጥራት፣ በተጠናከረ የኢንዱስትሪ ትስስርና ተፈላጊ ሙያተኞችን በማፍራት በክልሉ ኢኮኖሚ ላይ ተጨባጭ ለውጥ እንዲያመጡ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ አስታወቀ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ313 ሺህ በላይ የሁለተኛ ደረጃ ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ተሰራጭቷል – የክልሉ ግብርና ቢሮ