በጎነት የህሊና እርካታ ይሰጣል – በጎ አድራጊ ወጣቶች
ሀዋሳ: ጳጉሜ 03/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጎ ማድረግ የህሊና እርካታ የሚሰጥ በመሆኑ ሰዎች ለበጎ ሥራ ሊነሳሱ እንደሚገባ በቡታጅራ ከተማ በጎ አድራጊ ወጣቶች ተናግረዋል::
በቡታጅራ ከተማ ጳጉሜ 03 ቀን 2015 ዓ.ም የበጎነት ቀን በሚል በተለያዩ በጎ ተግባራት ተከብሮ ውሏል::
የከተማ ፅዳት ሥራ ሲያከናውኑ ያገኘናቸው የከተማዋ ወጣቶች መልካም ማድረግ እና በጎ ተግባር መፈፀም ካሳደጉን ወላጆቻችን የተማርነው ነገር ነው ብለዋል::
ይህ በጎ ሥራ በምንም ሊተካ የማይችልና የመንፈስ እርካታ የሚያስገኝ መሆኑን ገልጸዋል::
ዛሬ በመላ ኢትዮጵያ በሚከበረው የበጎነት ቀን ላይ ይህን ተግባር መፈፀም በመቻላችን ደስተኞች ነን ሲሉ ተናግረዋል::
ሌሎችም ወጣቶች መሠል ተግባራትን በማድረግ ለራሳቸውም ሆነ ለሌላ ሠው የደስታ ምንጭ መሆን እንደሚችሉ ጠቁመዋል::
የቡታጅራ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ አቶ አማን በድሩ በበጎነት ቀን የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛል ብለዋል::
የከተማ ፅዳት፣ የአልባሳት ድጋፍ፣ የደብተር ድጋፍና የእስክርቢቶ ድጋፍ እንዲሁም የአረጋዊያን ቤቶችን የማደስና ማዕድ የማጋራት ሥራ የመርሀግብሩ አካል ናቸው ብለዋል::
በተለይ ወጣቱ ለበጎ ሥራ እያሳየ ያለው ተነሳሽነት የሚደነቅ ነው ያሉት ምክትል ሃላፊው ላከናወኑት መልካም ተግባርም ምስጋና አቅርበዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ

More Stories
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግብርና ቢሮ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በክልሉ ለሚገኙ የዘርፉ ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ