የሳውላ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ
በደቡብ ክልል በጎፋ ዞን ለሚገነባው የሳውላ አዳሪ ትምህርት ቤት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ።
የመሠረት ድንጋዩን ያስቀመጡት የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ አቶ ተስፋዬ ቤልጅጌና ሌሎች የፌዴራልና የደቡብ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ስለመሆናቸው የኢዜአ መረጃ ያመለክታል።
ትምህርት ቤቱ በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ያስችላሉ ተብለው ከተያዙ 50 አዳሪ ትምህርት ቤቶች አካል ሲሆን፣ ከትምህርት ቤቶቹ መካከል 5ቱ በደቡብ ክልል እንደሚገነቡ ታውቋል።
ትምህርት ቤቱ በአንድ ዓመት ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ በ2017 ዓ.ም የመማር ማስተማር ስራ ይጀመርበታል ተብሏል።
የትምህርት ቤቱን ግንባታ ወጪ ሰዎች ለሰዎች የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት እንደሚሸፍን ተገልጿል።

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ