የሳውላ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ
በደቡብ ክልል በጎፋ ዞን ለሚገነባው የሳውላ አዳሪ ትምህርት ቤት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ።
የመሠረት ድንጋዩን ያስቀመጡት የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ አቶ ተስፋዬ ቤልጅጌና ሌሎች የፌዴራልና የደቡብ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ስለመሆናቸው የኢዜአ መረጃ ያመለክታል።
ትምህርት ቤቱ በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ያስችላሉ ተብለው ከተያዙ 50 አዳሪ ትምህርት ቤቶች አካል ሲሆን፣ ከትምህርት ቤቶቹ መካከል 5ቱ በደቡብ ክልል እንደሚገነቡ ታውቋል።
ትምህርት ቤቱ በአንድ ዓመት ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ በ2017 ዓ.ም የመማር ማስተማር ስራ ይጀመርበታል ተብሏል።
የትምህርት ቤቱን ግንባታ ወጪ ሰዎች ለሰዎች የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት እንደሚሸፍን ተገልጿል።

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ