በኮሬ ዞን የጽናት ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው
ዘመናዊ ቁመና፣ በሰው ኃይልና ቴክኖሎጂ ያደገበትን አቅም ማሳየትና ለሀገረ-መንግሥቱ ዘላቂነትና ለሕዝብ ሰላም የተከፈለውን የጀግኖች መስዋዕትነትን በመዘከር ነው የጽናት ቀኑ እየተከበረ የሚገኘው።
በዕለቱ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኮሬ ዞን አስተዳዳሪ ተወካይና የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አገኘሁ በቀለ ለሀገረ-መንግሥቱ ዘላቂነትና ለሕዝብ ሰላም የተከፈለውን የጀግኖች መስዋዕትነትን በመዘከር የጽናት ቀኑ የሚታሰብበት ነው ብለዋል።
አክለውም በጀግና አባቶች ሉአላዊነቷ ተጠብቆ ዛሬ የምንኖርባትን ኢትዮጵያ ለቀጣይ ትውልድ ለማሻገር በጽናት መጋደል እንደሚጠበቅም አቶ አገኘሁ ተናግረዋል።
የጽናት ቀኑ የዞኑ አመራሮችና የፀጥታ አካላት በተገኙበት በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛል።
ዘጋቢ፡ ምርጫ መላኩ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
በኮሬ ዞን የጽናት ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው

More Stories
“የፅናት ቀን” በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እየተከበረ ነው
ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የጉራጌ ዞን አስተዳደር ህንፃ እየተመረቀ ነው
በማህበራት ተደራጅተው ወደ ስራ የገቡ ወጣቶች ተስፋ ሰጪ ውጤቶችን እያስመዘገቡ መሆኑ ተገለጸ