የደሬቴድ ዲጂታል ሚዲያ የሐምሌ 21/2015 ዓ.ም የዕለቱ ዋና ዋና ዜናዎች፡-

👉በ2015/16 የምርት ዘመን ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ከታቀደው 15 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል ማዳበሪያ ውስጥ 10 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች መሠራጨቱን የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ አስታወቁ።

👉የአሠራር ማሻሻያዎች፣ የአሠራር ቁጥጥር የተደረገባቸው እና ክፍተታቸው ታይቶ የተደገፉ የልማት ድርጅቶች ወደ ትርፍ መመለስ መጀመራቸውን የመንግሥት የልማት ድርጅቶችና ይዞታ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

👉በደቡብ ክልል እየተተገበረ ያለው የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት በኑሯችን ላይ ተጨባጭ ለውጥ አምጥቶልናል ሲሉ በጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።

👉በአውቶሞቲቭ ኢንቨስትመንት ዘርፍ እንደ ቮልስዋገን ያሉ አለም አቀፍ አምራቾች እንዲሳተፉና እንዲያለሙ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለፀ።

👉ተገልጋይን በሚያንገላቱ የመንግስት ሰራተኞች ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ሲል የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡

👉በተያዘው በጀት ዓመት 529 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር ገለጸ።

👉በደቡብ ኦሞ ዞን የቱርሚ ወይጦ 120 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት ግንባታ ሥራ ያለበት ችግር ተፈትቶ በተያዘለት ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ተጠየቀ።