የደሬቴድ ዲጂታል ሚዲያ የሐምሌ 21/2015 ዓ.ም የዕለቱ ዋና ዋና ዜናዎች፡-
👉በ2015/16 የምርት ዘመን ለአርሶ አደሩ ለማቅረብ ከታቀደው 15 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል ማዳበሪያ ውስጥ 10 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል ማዳበሪያ ለአርሶ አደሮች መሠራጨቱን የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ አስታወቁ።
👉የአሠራር ማሻሻያዎች፣ የአሠራር ቁጥጥር የተደረገባቸው እና ክፍተታቸው ታይቶ የተደገፉ የልማት ድርጅቶች ወደ ትርፍ መመለስ መጀመራቸውን የመንግሥት የልማት ድርጅቶችና ይዞታ አስተዳደር አስታወቀ፡፡
👉በደቡብ ክልል እየተተገበረ ያለው የፍራፍሬ ልማት ፕሮጀክት በኑሯችን ላይ ተጨባጭ ለውጥ አምጥቶልናል ሲሉ በጉራጌ ዞን የመስቃን ወረዳ አርሶ አደሮች ገለጹ።
👉በአውቶሞቲቭ ኢንቨስትመንት ዘርፍ እንደ ቮልስዋገን ያሉ አለም አቀፍ አምራቾች እንዲሳተፉና እንዲያለሙ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገለፀ።
👉ተገልጋይን በሚያንገላቱ የመንግስት ሰራተኞች ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ሲል የሲዳማ ክልል ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ፡፡
👉በተያዘው በጀት ዓመት 529 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር ገለጸ።
👉በደቡብ ኦሞ ዞን የቱርሚ ወይጦ 120 ኪሎ ሜትር የኮንክሪት አስፋልት ግንባታ ሥራ ያለበት ችግር ተፈትቶ በተያዘለት ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ተጠየቀ።

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ