በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ
የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር በዓለምአቀፍ ደረጃ ከጡት ካንሰር ቀጥሎ ገዳይ በሽታ በመሆኑ ነው በወረዳው ለሚገኙ ሴቶች የምርመራ ዘመቻው የተካሄደው።
በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተካልኝ ጥላሁን ከጤና ተቋም ራቅ ያሉ ሴቶች ህክምና እንዲያገኙ ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የምርመራ እና የልየታ ዘመቻ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በወረዳው ባሉ ሁሉም ቀበሌያት የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር፣ ሲኖግራፊ፣ የደም ግፊት እና የስኳር በሽታዎችን በዘመቻ መልክ በምርመራ የመለየት ሥራ እየሠሩ መሆናቸውንም ኃላፊው አስረድተዋል።
ግራውንድስ ፎር ሄልዝ አስተባባሪ አቶ መስፍን ዋና በበኩላቸው፣ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር በዓለም አቀፍ ደረጃ ከጡት ካንሰር ቀጥሎ ገዳይና አደገኛ በሽታ በመሆኑ ሴቶች በንቃት ተመርምረው ራሳቸውን ማወቅ እንዳለባቸው ገልጸዋል።
የአንዲት ሴት ሕይወት ዋጋ ስላላት በማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ላይ ትኩረት አድርገው እየሠሩ መሆናቸውን በመግለጽ ከልየታ በኋላ በጊዜ ህክምና የሚያገኙበት ሁኔታ መመቻቸቱን አስተባባሪው ጠቁመዋል።
በወረዳው የቆንጋ ጤና ጣቢያ እና የብርብስ ቄላ ጤና ኬላ ባለሙያዎች ወይዘሮ አበበች ባፋ እና መሠረት ታደሰ እንደተናገሩት፤ የምርመራው ሂደት ቀድሞ ከነበረው የተለየ በመሆኑ በቀላሉ መጨረስ እንደሚቻል ነው የገለጹት።
በማህበረሰቡ የግንዛቤ ዕጥረት በመኖሩ ወደ ጤና ጣቢያ በመሄድ እንዲመረመሩ የቅስቀሳ ሥራ እያከናወኑ መቆየታቸውን ያነሱት ባለሙያዎቹ በዚህም በርካታ ሴቶች ተጠቃሚ መሆናቸውን አስረድተዋል።
ምርመራ ሲያደርጉ አግኝንተን ያነጋገርናቸው ወይዘሮ ፀሐይነሽ እሸቱ፣ ዘለቀች ባርሳ እና ሌሎችም የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ አካባቢያቸው ላይ በመምጣቱ መደሰታቸውን በመግለጽ ምርመራው ራስን በማወቅ ቶሎ ህክምና ለማግኘት እንደሚረዳቸውም ተናግረዋል።
ዘጋቢ: አሀዱ አሸናፊ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር ምርመራ እና ልየታ ተካሄደ

More Stories
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ኃላፊና የየዞን ከፍተኛ አመራሮች በሣውላ ማረሚያ ተቋም አረንጓዴ አሻራቸውን በማኖር ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ
በሁሉም ዘርፍ የተመዘገቡ ውጤቶችን በማስቀጠል የምክር ቤት አባላት የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተገለጸ
የአርሶ አደሩን የመሬት ሀብት ከፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ጋር በማስተሳሰር አርሶአደሩ የፋይናንስ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ