የሰላም ሚኒስቴር እና የብሄራዊ ተሃዲሶ ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች በጉራጌ ዞን ማረቆ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት በጎ ፈቃድ አግልግሎት አስጀመሩ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሰላም ሚኒስቴር እና የብሄራዊ ተሃዲሶ ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች በጉራጌ ዞን ማረቆ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት በጎ ፈቃድ አግልግሎት በዛሬው ዕለት አስጀምረዋል።
አመራሮችና ሠራተኞቹ “ነገን ዛሬ እንትከል” በሚል መሪ ሀሳብ እንደ ሀገር እየተካሄደ ያለውን የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም የሚያጠናክር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አድርገዋል።
የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንዳአ ከብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተወካይ አቶ ሻንቆ ደሳለኝ ጋር በመሆን 100 ለሚሆኑ የኢኮኖሚ አቅም ውስንነት ላለባቸው ቤተሰብ የተማሪዎች የትምህርት ግብአቶችን ድጋፍ ያበረከቱ ሲሆኑ ለ50 አረጋዊያን ደግሞ ጋቢ አልብሰዋል።
የአቅማ ደካሞችን ቤት ለማደስና የቆሼ ሽግግር የመጀመሪያ ደረጀ ትምህርት ቤት ለማስፋፋትም ቃል ገብተዋል።
የቤት እድሳቱ በአጭር ጊዜ ተጠናቅቆ ለተጠቃሚዎቹ እንዲተላለፍ የቅርብ ክትልል እንደሚያደርጉም አመራሮቹ አረጋግጠዋል፡፡
የማረቆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጉሴ መኬ በበኩላቸው ከአዲስ አበባ 156 ኪሎ ሜትር ተጉዘው በመምጣት በወረዳው ላደረጉት በጎ ተግባር አመስግነዋል።
የሰላም ሚኒስቴርና የብሂራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ሠራተኞችና አመራሮች የተከሏቸው ችግኞች እንዲፀድቁ ተገቢውን የእንክብካቤና ጥበቃ ሥራዎች እንደሚሠሩም አረጋግጠዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ

More Stories
የአካባቢ ብክለትን እና የካርበን ልቀትን ከመከላከል ባሻገር ለታዳሽ ሀይል ትኩረት ሊደረግ ይገባል – የክልሉ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን
በዩኒቨርሲቲው በምርምር እና በቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ከጊዜ ወደ ጊዜ ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው ተገለፀ
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሕብረተሰቡ በነፃነት ተሳትፎ ያደረገበት መሆኑ ተገለጸ