የሰላም ሚኒስቴር እና የብሄራዊ ተሃዲሶ ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች በጉራጌ ዞን ማረቆ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት በጎ ፈቃድ አግልግሎት አስጀመሩ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 20/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሰላም ሚኒስቴር እና የብሄራዊ ተሃዲሶ ኮሚሽን አመራሮችና ሠራተኞች በጉራጌ ዞን ማረቆ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት በጎ ፈቃድ አግልግሎት በዛሬው ዕለት አስጀምረዋል።
አመራሮችና ሠራተኞቹ “ነገን ዛሬ እንትከል” በሚል መሪ ሀሳብ እንደ ሀገር እየተካሄደ ያለውን የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም የሚያጠናክር የችግኝ ተከላ ፕሮግራም አድርገዋል።
የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንዳአ ከብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተወካይ አቶ ሻንቆ ደሳለኝ ጋር በመሆን 100 ለሚሆኑ የኢኮኖሚ አቅም ውስንነት ላለባቸው ቤተሰብ የተማሪዎች የትምህርት ግብአቶችን ድጋፍ ያበረከቱ ሲሆኑ ለ50 አረጋዊያን ደግሞ ጋቢ አልብሰዋል።
የአቅማ ደካሞችን ቤት ለማደስና የቆሼ ሽግግር የመጀመሪያ ደረጀ ትምህርት ቤት ለማስፋፋትም ቃል ገብተዋል።
የቤት እድሳቱ በአጭር ጊዜ ተጠናቅቆ ለተጠቃሚዎቹ እንዲተላለፍ የቅርብ ክትልል እንደሚያደርጉም አመራሮቹ አረጋግጠዋል፡፡
የማረቆ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ንጉሴ መኬ በበኩላቸው ከአዲስ አበባ 156 ኪሎ ሜትር ተጉዘው በመምጣት በወረዳው ላደረጉት በጎ ተግባር አመስግነዋል።
የሰላም ሚኒስቴርና የብሂራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ሠራተኞችና አመራሮች የተከሏቸው ችግኞች እንዲፀድቁ ተገቢውን የእንክብካቤና ጥበቃ ሥራዎች እንደሚሠሩም አረጋግጠዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ጌታሁን አንጭሶ

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ