የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በሀላባ ዞን የመስክ ምልከታ ማድረግ ጀመረ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በሀላባ ዞን የመስክ ምልከታ ማድረግ ጀመረ

በምክር ቤቱ የፕላን መሰረተ ልማትና የመንግስት ሀብት ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሰቢ አቶ ታመነ ገብሬ የመሩት የቅኝት ቡድን በሀላባ ከቶቲ ኡሎ ወረዳ የተለያዩ ስራዎችን እየተመለከቱ ነው።

ቋሚ ኮሚቴው በአቶቲ ኡሉ ወረዳ የቆልቻ 2 ድልድይ፣ በዌራ ዲጆ ወረዳ የሌጋሞ ድልድይ፣ እንዲሁም ቆቦ ማዞሪያ-ቆቦ-አሻሻሬ የገጠር መንገድ የግንባታ ሂደትን ተመልክቷል።

ቋሚ ኮሚቴው በቀጣይ ቀናትም በክልሉ የተለያዩ ዞኖች በመንግስት እየተሰሩ ያሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ተዟዙሮ ይመለከታል።

ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ