በቤንች ሸኮ ዞን ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 27/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቤንች ሸኮ ዞን ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛው ሀይሌ እንደተናገሩት፥ በዞኑ ከትላንት ጀምሮ ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ያለምንም ችግር በሰላም መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ የተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ሰፊ መሆናቸውን ተከትሎ በፈተና ጣቢያዎች ላይ የተቀመጡ አዳዲስ አሰራሮችና የተደረጉ ክልከላዎች ለፈተናው ስኬታማነት አጋዥ ነበሩ ብለዋል።
ከዚህ በተጓዳኝ በየደረጃው የሚገኙ የፀጥታና የትምህርት ባለድርሻ አካላት ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦ አቶ ግዛው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በዞኑ የሚገኙ ተማሪዎች ፈተናውን በተገቢው መንገድ አንብበውና ተረጋግተው የወሰዱ ሲሆን ከኩረጃ በፀዳ መልኩ መከናወኑንም ጠቁመዋል።
በዞኑ በ2015 ዓ.ም በ200 ፈተና ጣቢያዎች ላይ 11ሺህ 800 በላይ ተማሪዎች ክልላዊ ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን
More Stories
የኢፌዲሪ ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ በጉራጌ ዞን ምሁር አክሊል ወረዳ መቆርቆር ቀበሌ ያስገነባው የንጹህ መጠ ውሃ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
የኡዱሂያ የዕርድ ስርዓት….የአብሮነት ነፀብራቅ
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ