በቤንች ሸኮ ዞን ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 27/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቤንች ሸኮ ዞን ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛው ሀይሌ እንደተናገሩት፥ በዞኑ ከትላንት ጀምሮ ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ያለምንም ችግር በሰላም መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ የተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ሰፊ መሆናቸውን ተከትሎ በፈተና ጣቢያዎች ላይ የተቀመጡ አዳዲስ አሰራሮችና የተደረጉ ክልከላዎች ለፈተናው ስኬታማነት አጋዥ ነበሩ ብለዋል።
ከዚህ በተጓዳኝ በየደረጃው የሚገኙ የፀጥታና የትምህርት ባለድርሻ አካላት ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦ አቶ ግዛው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በዞኑ የሚገኙ ተማሪዎች ፈተናውን በተገቢው መንገድ አንብበውና ተረጋግተው የወሰዱ ሲሆን ከኩረጃ በፀዳ መልኩ መከናወኑንም ጠቁመዋል።
በዞኑ በ2015 ዓ.ም በ200 ፈተና ጣቢያዎች ላይ 11ሺህ 800 በላይ ተማሪዎች ክልላዊ ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን
More Stories
ተቋም የህግ ታራሚዎች የሰብዓዊ መብት አያይዝ የተሻለ መሆኑን የአሪ ዞን ፍትህ መምርያ አስታወቀ
ጠንካራ የጤና ልማት ስርአት በመዘርጋት የህብረተሰቡን የጤና አገልግሎት ጥራት እና ተደራሽነትን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ
በቡና ኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች የውሃን ሀብት ከብክለት በመጠበቅ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ የጌዴኦ ዞን ግብርና መምሪያ አሳሰበ