በቤንች ሸኮ ዞን ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 27/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቤንች ሸኮ ዞን ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛው ሀይሌ እንደተናገሩት፥ በዞኑ ከትላንት ጀምሮ ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ያለምንም ችግር በሰላም መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ የተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ሰፊ መሆናቸውን ተከትሎ በፈተና ጣቢያዎች ላይ የተቀመጡ አዳዲስ አሰራሮችና የተደረጉ ክልከላዎች ለፈተናው ስኬታማነት አጋዥ ነበሩ ብለዋል።
ከዚህ በተጓዳኝ በየደረጃው የሚገኙ የፀጥታና የትምህርት ባለድርሻ አካላት ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦ አቶ ግዛው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በዞኑ የሚገኙ ተማሪዎች ፈተናውን በተገቢው መንገድ አንብበውና ተረጋግተው የወሰዱ ሲሆን ከኩረጃ በፀዳ መልኩ መከናወኑንም ጠቁመዋል።
በዞኑ በ2015 ዓ.ም በ200 ፈተና ጣቢያዎች ላይ 11ሺህ 800 በላይ ተማሪዎች ክልላዊ ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በመሎ ኮዛ ምርጫ ክልል በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ድምፅ መስጠት ተጀመረ
በካፋ ዞን ቢጣ ጌሻ ሞርጫ ክልል መራጮች ድምጽ መስጠት ጀምረዋል፡፡
ለተከታታይ 7 ምርጫዎች የተሳተፉ የጃጁራ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች