በቤንች ሸኮ ዞን ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁ ተገለጸ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 27/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቤንች ሸኮ ዞን ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን የዞኑ ትምህርት መምሪያ አስታወቀ።
የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ግዛው ሀይሌ እንደተናገሩት፥ በዞኑ ከትላንት ጀምሮ ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ያለምንም ችግር በሰላም መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ የተደረጉ ቅድመ ዝግጅቶች ሰፊ መሆናቸውን ተከትሎ በፈተና ጣቢያዎች ላይ የተቀመጡ አዳዲስ አሰራሮችና የተደረጉ ክልከላዎች ለፈተናው ስኬታማነት አጋዥ ነበሩ ብለዋል።
ከዚህ በተጓዳኝ በየደረጃው የሚገኙ የፀጥታና የትምህርት ባለድርሻ አካላት ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽኦ አቶ ግዛው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በዞኑ የሚገኙ ተማሪዎች ፈተናውን በተገቢው መንገድ አንብበውና ተረጋግተው የወሰዱ ሲሆን ከኩረጃ በፀዳ መልኩ መከናወኑንም ጠቁመዋል።
በዞኑ በ2015 ዓ.ም በ200 ፈተና ጣቢያዎች ላይ 11ሺህ 800 በላይ ተማሪዎች ክልላዊ ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
በቀቤና ልዩ ወረዳ የሚገነቡት የኢማም ሀሰን ኡንጀሞ ሆስፒታል እና የፈትሁዲን ላሉተ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ መሆናቸውን ተገለፀ
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ