ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ ቡናን አሸነፈ
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ በተካሄደው የሸገር ደርቢ ቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ ቡናን 1ለ0 በማሸነፍ አዲሱን የውድድር ዓመት በድል ጀምሯል።
ከስድስት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለቱ ክለቦች በፕሪሚዬር ሊጉ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተገናኙበት ጨዋታ የቅዱስ ጊዮርጊስን ወሳኝ የማሸነፊያ ጎል አቤል ያለው በ66ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፏል።
በጨዋታው የኢትዮጵያ ቡናው ግብ ጠባቂ ዳላንድ ኢብራሂም አቤል ያለው ጥፋት መስራቱን ተከትሎ በ53ኛው ደቂቃ በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል።
ቅዱስ ጊዮርጊስ በቀጣይ የሊጉ መርሐግብር ከኢትዮጲያ መድህን ጋር የፊታችን ቅዳሜ ሲጫወት ኢትዮጵያ ቡና ደግሞ ከነገሌ አርሲ ጋር በመጪው ሀሙስ የሚጫወት ይሆናል።
ዘጋቢ፡ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንዳጠናቀቅን ሁሉ የባህር በርን ለማስመለስ የሚደረገውን ጥረት በይበልጥ ማገዝ እና መደገፍ እንደሚገባ ተጠቆመ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ከፌደራል ገንዘብ ሚኒስቴር እና ከክልሉ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ዙሪያ ለኦዲት ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል
ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ