ይህ የተገለፀው የዞኑ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና በ2018 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር ባካሄደው የውይይት መድረክ ላይ ነው፡፡
በዞኑ የንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት እጥረትን ለመቅረፍ የሚከናወኑ ተግባራትን በመደገፍ ግብረሰናይ ድርጅቶች ላበረከቱት አስተዋጽኦ የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ ታጠቅ ዶሪ (ዕጩ ዶ/ር) አመስግነዋል፡፡
ምክትል አስተዳዳሪው አክለውም አሁን ያለንበት ወቅት የቡና ምርት የሚሰበሰብበት በመሆኑ በታጠበ ቡና ዘርፍ የተሰማሩ ባለሀብቶች የውሃ ሀብትን ከብክለት በመጠበቅ ማህበራዊ ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል፡፡
በውይይት መድረኩ የጌዴኦ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ኢንጂነር ተመስገን ጥላሁን፤ የማዕድን አማራጮችን በጥናት ለይቶ ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ይገባል ብለዋል፡፡
በዘርፉ በህገወጥ መንገድ በመሰማራት ለጥቅማቸው ሲሉ የህዝብንና የመንግስትን ሀብት የሚያባክኑ አካላት ላይ የእርምት እርምጃ ለመውሰድ ህብረተሰቡ ለህግ አስከባሪዎች ጥቆማ በመስጠት የበኩሉን እንዲወጣ ኢንጂነር ተመስገን አሳስበዋል፡፡
የጌዴኦ ዞን 48 የሚፈሱ ወንዞችና በርካታ ገጸ ምድርና ከርሰ ምድር ውሃ የተፈጥሮ ፀጋ የተቸረው እንደሆነ የዞኑ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ ዳዊት ጀቦ (ዶ/ር) በመናገር፤ በዚህም አርሶአደሩ ከዝናብ ጠባቂነት በመውጣትና የመስኖ አማራጮችን በመጠቀም እንዲያመርት በበጀት ዓመቱ በትኩረት እንደሚሠሩ ጠቁመዋል፡፡
በ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም የተሻለ ውጤት እዲመዘገብ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሴክተር መስሪያ ቤቱ ባለሙያዎች፣ ግብረሰናይ ድርጅቶችና ድጋፍ ላደረጉ ተቋማት እውቅናና የሽልማት ፕሮግራም በማጠቃለያው ተካሂዷል፡፡
ዘጋቢ፡ ውብሸት ኃ/ማርያም – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን

More Stories
የታላቁ ህዳሴ ግድብን እንዳጠናቀቅን ሁሉ የባህር በርን ለማስመለስ የሚደረገውን ጥረት በይበልጥ ማገዝ እና መደገፍ እንደሚገባ ተጠቆመ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፋይናንስ ቢሮ ከፌደራል ገንዘብ ሚኒስቴር እና ከክልሉ አመራር አካዳሚ ጋር በመተባበር በመንግስት ፋይናንስ አስተዳደር ዙሪያ ለኦዲት ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል
ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ