የሩቅ ምስራቋ ሀገር ጃፓን በእግርኳሱ የዓለማችን ሀያል የሆነችውን ብራዚል በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ መርታት ችላለች።
ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች በአቋም መለኪያ ጨዋታ ዛሬ ተገናኝተው ጃፓን ከ2ለ0 መመራት ተነስታ 3ለ2 በማሸነፍ ታሪካዊ ድልን በብራዚል ላይ ተቀዳጅታለች።
በጨዋታው ፓውሎ ሄንሪኬ በ26ኛው ደቂቃ እና ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ32ኛው ደቂቃ ጎሎችን በማስቆጠር ሴሌሳዎቹ 2ለ0 እየመሩ ለእረፍት ወደ መልበሻ ክፍል አምርተው ነበር።
ነገር ግን በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪካቸው ከጥሎ ማለፉ ተሻግረው የማያውቁት ጃፓኖች በሁለተኛው አጋማሽ 3 ጎሎችን አከታትለው በማስቆጠር ውጤቱን ቀልብሰውታል።
በአሰልጣኝ ሃጂሜ ሞዪረሱ ለሚመሩት ጃፓኖች ታሪካዊ የድል ግቦችን የቀድሞ የሊቨርፑሉ አማካይ ታኩሚ ሚናሚኖ በ52ኛው ደቂቃ፣ ኬይቶ ናካሙራ በ62ኛው ደቂቃ እና አሳዬ ኡኤዳ በ71ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፈዋል።
ጃፓን እና ብራዚል ከአሁን ቀደም 9 ጊዜ የተገናኙ ሲሆን ብራዚል 9 ጊዜ ስታሸንፍ 2 ጊዜ ደግሞ አቻ ነበር የተለያዩት።
ዘጋቢ፡ ሙሉቀን ባሳ

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ