የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ አጠናክረን የምናስቀጥልበት ነው ሲሉ የቀቤና ልዩ ወረዳ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ተናገሩ
ሀዋሳ፣ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ አጠናክረን የምናስቀጥልበት ነው ሲሉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ፈቱዲን ሙዘሚል ተናግረዋል፡፡
በልዩ ወረዳው 18ኛዉ የሰንደቅ አላማ ቀን በፖናል ውይይትና በልዩ ልዩ ዝግጅቶች በወልቂጤ ከተማ ተከብሯል።
የቀቤና ልዩ ወረዳ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ፈቱዲን ሙዘሚል እንደተናገሩት ሰንደቅ አላማ ለብሄራዊ አንድነት እና ሉዓላዊነት እንዲሁም ለኢትዮጵያ የከፈታ ዘመን ብስራት ነው ።
የሰንደቅ አላማ ክብረ በዓል ዋነኛው አላማ የህግ የበላይነትን በማክበር እና በማስከበር የፍትህ ስርዓትን ማስጠበቅ እንደሆነ አስረድተዋል።
ለሀገር አንድነት እና ሉዓላዊነት መፅናት አስተማማኝ ብሄራዊ መግባባት ወሳኝ ነው ያሉት አፈ ጉባኤው ሰንደቅ አላማችን የሀገር ሉዓላዊነት እና የህዝባችን የአንድነት መገለጫ እንደሆነ ተናግረዋል።
በዓሉ ሀገራዊ ስሜትና እንድነት እንዲጎለብት የሚያስችል መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የበዓሉ ተሳታፊዎች ናቸው ፡፡
ተሳታፊዎቹ ሁሉም በተሰማራበት የስራ መስክ ጠንክሮ በመስራት የሀገሪቱ ብልፅግና ለማረጋገጥ መትጋት እንደሚገባው ገልፀዋል ፡፡
በበዓሉ የልዩ ወረዳው አመራሮች የፖሊስ አባላት የመንግስት ሰራተኞች እና ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተው በህብረት የኢትዮጵያ ብህራዊ መዝሙር በመዘመር እና ሰንደቅ አላማ የመስቀል ስነ-ስርዓት ተከናውኗል ።
ዘጋቢ፦ ወለላ ኤልያስ ከወልቂጤ ጣቢያችን

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ