የሀገር ሉዓላዊ ክብር መገለጫ ለሆነዉ ሰንደቅ ዓላማ ተገቢዉን ክብር መስጠት እንደሚገባ የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በዛሬዉ ዕለት 18ኛዉ የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች በድምቀት ተከብሯል።
በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ናዝሬት ዘኪዎስ እንደገለፁት፤ 18ኛዉ የሰንደቅ ዓላማ ቀን የዘመናት ቁጭት ሆኖ የቆየው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ ማግስት የሚከበር መሆኑ ከሌሎች ጊዜያት ለየት ያደርገዋል።
የወረዳው ነዋሪዎችም ሀገራችን ለጀመረችዉ ሁለንተናዊ ዕድገት እያበረከቱ ያሉትን ድጋፍ ይበልጥ አጠናክረው ማስቀጠል እንዳለባቸዉ ዋና አፈ ጉባኤዋ አሳስበዋል።
የሰንደቅ ዓላማ ቀለማት የኢትዮጰያዊያን ጀግንነት መስዕዋትነት እንዲሁም የልማት አርበኝነት ማሳያ ናቸው ያሉት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ቡኔ፤ ለትናንሽ አጀንዳዎች ጆሮ ባለመስጠት ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ማሻገር ይገባል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና ነጻነት በቀደምት አባቶች ደምና አጥንት ላይ የቆመ ነው ያሉት አቶ ዳዊት ደህም፤ ትውልድ የታሪካዊ ሃገሩን ክብር የመጠበቅ አደራ አለበት ብለዋል፡፡
የሀገራችን ሉዓላዊነት መገለጫ የሆነዉን የሰንደቅ ዓላማ ቀንን ስናከብር ጀግኖች አባቶቻችን ላቆዩት ሀገርና ሰንደቅ ዓላማ ተገቢዉን ክብር በመስጠት ሊሆን እንደሚገባም አስተዳዳሪው አስገንዝበዋል።
የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል በፖሊስ ሰልፍ ትርዕይት፣ በሰንደቅ ዓላማ መስቀል ሥነ-ሥርዓት፣ መሪ ቃልና መልዕክቶችን በማስተጋባት እንዲሁም በሌሎች ልዩ ልዩ ዝግጅቶች በልዩ ድምቀት ተከብሯል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የወረዳ አመራሮች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ የፀጥታ አስከባሪዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ: ዘርሁን ሹፌር – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
የሀገር ሉዓላዊ ክብር መገለጫ ለሆነዉ ሰንደቅ ዓላማ ተገቢዉን ክብር መስጠት እንደሚገባ የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ

More Stories
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል
በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የምግብ ዋስትና ፕሮጀክት እየተስተዋለ ያለውን ድህነት እና የስራ አጥነት ችግር ለመቅረፍ ያበረከተው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑ ተገለጸ