ሰንደቅ ዓላማ ለአንድ ሀገር መለያ፣ የሉዓላዊነትና የነፃነት ዓርማ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ገለፀ
18ኛው የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን ”ሰንደቅ ዓላማ ለኢትዮጵያ ታላቅ ከፍታ ዘመን ብስራት፤ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉአዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ” በሚል መሪ ቃል በአርባ ምንጭ ከተማ ተከብሯል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ወላይቴ ቢተው እንደገለጹት፤ ሰንደቅ ዓላማ ለአንድ ሀገር መለያ ብቻ ሳይሆን የሉዓላዊነትና የነፃነት ዓርማ ነው።
ሰንደቅ ዓላማ የህዝባችን አንድነትና አብሮነት ምልክት፣ ጀግኖች ለክብሯ የተዋደቁላት፣ ለጥቁር ህዝቦች የነፃነትና የአይበገሬነት ምልክት ለሆነች ታላቅና ታሪካዊ ሀገር የተወከለችበት ዓርማ ነው።
ሰንደቅ ዓላማ ሀገራዊ አንድነትና አብሮነት ማጠናከሪያ በመሆኑ የሀገር ልማትንና ብልጽግናን የሚያስቀጥል እንዲሁም የሀገሪቱን ብሎም የክልሉን ህዝብ ሰላምና አንድነት ማስቀጠያ መሆኑንም አስረድተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኦዲት መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር አቶ አበባየሁ ኤርምያስ፤ የዘንድሮው ሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተጠናቀቀ ማግስት መከበሩ የዘንድሮውን ሰንደቅ ዓላማ ቀን ልዩ የሚያደርግ መሆኑን አብራርተዋል።
አቶ አበባየሁ አክለውም፤ የትናንት ፈተናን፣ አንድነት በመፍጠር በድል እንደተሻገርን ሁሉ የቀጣዩንም ለመሻገር አንድነትን መፍጠር ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
የስንደቅ ዓላማን ምንነትንና ክብር ከማስረጽ አኳያ ሁሉም ባለድርሻ አካል የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል።
አስተያየታቸውን ከሰጡን መካከል ሳጂን ሰራዊት ኡቴ እና ረዳት ኢንስፔክተር ኤፍሬም መስፎ፤ሰንደቅ ዓላማ ለኢትዮጵያ ከፍታና ሉዓላዊነት የተከፈለ የመስዋዕትነት ምልክት መሆኑን ገልጸዋል።
መርሀ ግብሩ ሰንደቅ ዓላማ በመስቀል እና በሰንደቅ ዓላማ ፊት ቃለ መሐላ በመፈፀም ተቋጭቷል።
ዘጋቢ፡ አስናቀ ካንኮ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
ሰንደቅ ዓላማ ለአንድ ሀገር መለያ፣ የሉዓላዊነትና የነፃነት ዓርማ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ገለፀ

More Stories
በጎፋ ዞን የደምባ ጎፋ ወረዳ ጤና ጽህፈት ቤት የጉበት በሽታ መከላከያ ክትባት ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ
የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል የኢትዮጵያን የከፍታ ጉዞ አጠናክረን የምናስቀጥልበት ነው ሲሉ የቀቤና ልዩ ወረዳ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ተናገሩ
ለአጠቃላይ ትምህርት ጥራት የቅድመ አንደኛ ላይ ትኩረት ማድረግ ሁሉም አካል ሊረባረብ እንደሚገባ ተገለጸ