ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ቃል በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል።
ዕለቱን አስመልክቶ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ዮሐንስ ካሳሁን እንደገለፁት፤ ሠንደቅ ዓላማ የሀገር አንድነት መገለጫ የህብረ ብሔራዊ አንድነት ኩራት ነው።
ለመላው የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምልክት የሆነውን ሠንደቅ ዓላማ ክብሩን አስጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ ከሁሉም ኢትዮጵያዊያን ይጠበቃል ብለዋል።
“ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት የክልሉ ብሄረሰቦች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ መሰለ ከበደ፤ ሠንደቅ ዓላማ የሀገራዊ አንድነትና የነፃነት መገለጫ ታላቅ የብሔራዊ ኩራት አርማ እንደሆነ ገልፀዋል።
ሠንደቅ ዓላማ በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ቦታ ተሰጥቶት የሚከበር ታላቅ ሀገራዊ በዓል መሆኑን ያነሱት የበዓሉ ተሳታፊዎች፤ ለሠንደቅ ዓላማ ክብር በአንድነት መቆም ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል።
ዕለቱ ሠንደቅ ዓላማ በመስቀልና በሠንደቅ ዓላማ ፊት ቃለ መሐላ በመፈፀም በድምቀት ተከብሯል።
በበዓሉ ላይ የክልሉ ብዝሃ ማዕከል ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች፣ የሸካ ዞን አመራሮች፣ የመንግሥት ሰራተኞችን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የፀጥታ አካላት ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ: አስቻለው አየለ – ከማሻ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ