ምክር ቤቱ 25ኛ መደበኛ ጉባዔውን ያካሂዳል
ሀዋሳ፡ ሰኔ 15/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባዔ ዛሬ ይካሄዳል፡፡
ምክር ቤቱ ዛሬ በሚያካሂደው 25ኛ መደበኛ ጉባዔው የ24ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤን መርምሮ የሚያፀድቅ ይሆናል፡፡
የምክር ቤቱ ቀጣይ አጀንዳ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ክፍያን ለመወሰን እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የሠራተኞች አስተዳደር ረቂቅ ደንብን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ እንደሚመራ ይጠበቃል፡፡
ምንጭ ፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
More Stories
ከ5 መቶ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሮች እየተሰራጨ መሆኑ ተገለጸ
የትራንስፖርት ዘርፍ አገልግሎቱን ለማዘመን ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አስታወቀ
የትምህርት አጀንዳ “የሁሉም ልማት በኩር አጀንዳ ነው” ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ገለፁ