ምክር ቤቱ 25ኛ መደበኛ ጉባዔውን ያካሂዳል
ሀዋሳ፡ ሰኔ 15/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ ዓመት የስራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ጉባዔ ዛሬ ይካሄዳል፡፡
ምክር ቤቱ ዛሬ በሚያካሂደው 25ኛ መደበኛ ጉባዔው የ24ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤን መርምሮ የሚያፀድቅ ይሆናል፡፡
የምክር ቤቱ ቀጣይ አጀንዳ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ክፍያን ለመወሰን እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የሠራተኞች አስተዳደር ረቂቅ ደንብን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ እንደሚመራ ይጠበቃል፡፡
ምንጭ ፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

More Stories
በቀቤና ልዩ ወረዳ የሚገነቡት የኢማም ሀሰን ኡንጀሞ ሆስፒታል እና የፈትሁዲን ላሉተ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን የዘመናት የልማት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ መሆናቸውን ተገለፀ
በክልሉ ባለፉ 6 ወራት ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰብ መቻሉ ተገለፀ
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት የህግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ የክልሉን ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የግማሽ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገመገመ