የባህል እሴቶችን እና ሀገር በቀል እውቀቶችን በስፋት ማስተዋወቅ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ ።
በዚህ ዙርያ በከልሉ ለማገኙት ሙያተኞች ና ለባለ ድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጥቷል ።
በስልጠናው ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ባህል ፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፈንታሁ ብላቴ የብሄር ብሄረሰቦች ና ህዝቦች ቱባ ባህላዊ ዕሴቶች ሀገር በቀል ዕውቀቶች ና የባህል ተምሳሌቶችን በተደራጀ መልኩ ለማስታወቅ ሚቹ መድረክ ለመፈጠር የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን አብራርተዋል ።
በዘርፉ ለተሰማሩት ባለሀብቶች ፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ፤ ሙያ ማህበራት ኢንተርፕራይዞች ፣ ወጣቶችና ሴቶች ለልምድ ልውውጥ የስራ ዕድልና የገበያ ትስስር ለመፈጠር እንደሚረዳም አክለዋል ።
የቢሮ ምክትል ኃላፊ ና የባህልና ቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊ አቶ አክሊሉ ለማ በበኩላቸው የባህል ፌስቲቫል፣ ካርኒቫልና ኤግዚብሽን መካሄድ የክልሉን ብሄሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በተፈጥሮ የታደሉትን በታሪክ ያካበቱትን ቱባ ባህል ፣ እሴቶች ቋሚና ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን የኪነ-ጥበብና የዕደ-ጥበብ ትውፊቶችን ለማስተዋወቅ ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል ።
ወጣቱ ትውልድ የባህልን ልማታዊ አስተዋጽኦ ግንዛቤ ለመፈጠር በማንነቱ የሚኮራ ትዉልድ ለመፈጠር ጉልህ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።
ፌስቲቫል፣ካርኒቫል ና ኤግዚብሽን ስናካሂድ ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶችና አሉታዊ መጤ ባህሎችን ደረጃ በደረጃ በመቀነስ ብሎም በማስቀረት መሆን እንዳለበት ምክትል የቢሮ ኃላፊ አጽንኦት ሰጥተዋል ።
ስልጠናው በክልሉ ላሉት ከስድቱም ዞኖች ለተወጣጡ ለባህል ሙያተኞች ና ለባድርሻ አካላት የተሰጠ ሲሆን ከእነሱም መካከል አንዳንዶቹ በሰጡበት አስተያየት በየአካባቢያችን ፌስቲቫል፣ካርኒቫልና ኤግዚብሽን እጅግ የሚጠቅም ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል

More Stories
ከመማር ማስተማር ተግባር ባለፈ የአካባቢ ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን የሚዛን ግብርና ቴክኒክ ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኮሌጅ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ(ዶ/ር) መጭው ጊዜ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ብርሃን የምንሸጋገርበት ብሩህ ዘመን መሆኑን ተናገሩ
በተቀሩት አጭር ቀናት ህብረተሠቡ የመራጭነት ካርዱን በመውሰድ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ የጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳና አካባቢው የፌደራልና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጥሪ አቀረቡ