የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ምርጫ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከሐምሌ 10/2017 ጀምሮ እንደሚያካሂድ ተገለፀ
ምክር ቤቱ በዚሁ ጉባኤው በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ አጽንኦት ሰጥቶ እንደሚመክር ተገልጿል።
ከሐምሌ 10/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄደው 6ኛ ምርጫ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ ታሪካዊ ጉባኤ መሆኑን ነው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ የገለጹት።
ክልሉ በሁለት ዓመት ቆይታው ባከናወናቸው ተግባራት የታዩ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ ያከናወናቸው ስኬቶች ምን እንደሚመስሉ በስፋት ይታያሉ ነው ያሉት አቶ አለማየሁ።
በጉባኤው ላይ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የዋና ኦዲት መስሪያ ቤት ዕቅድ አፈፃፀም ቀርቦ በዋና ዋና ጉዳዮች በስፋት ውይይት ይካሄድባቸዋል ብለዋል ዋና አፈ ጉባኤው።
የህዝብን ዘላቂ ሰላም እንዲሁም ልማትን በሚያረጋግጡ እንዲሁም ህብረብሔራዊ አንድነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ጉባኤው ይመክራል ያሉት የክልሉ ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አለማየሁ ባውዲ፤ በ2017 ለተከናወኑ ስኬቶች ዕውቅናም እንደሚሰጥ አመላክተዋል።
የምክር ቤት አባላት የህዝብ ድምፅ ናቸው ያሉት ዋና አፈ ጉባኤው፤ ከዕቅድ ጀምሮ መሬት ላይ አፈፃፀሙ በትክክል ስለመውረዱና ህዝቡ የልማት ተጠቃሚ ሰለመሆኑ መከታተል ድርሻቸው እንደሆነም አመላክተዋል።
ከሐምሌ 10 ጀምሮ በሚካሄደው በዚሁ ጉባኤ ባለድርሻ አካላት እንደሚገኙና የቅድመ ዝግጅት ሥራው መጠናቀቁን ጭምር አቶ አለማየሁ ባውዲ አብራርተዋል።
ዘጋቢ፡ ታምሩ በልሁ – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን

More Stories
ዲግሪው “ወረቀት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ተስፋና የትውልድ ኃላፊነት ነው” – አፈወርቅ ካሱ (ፕ/ር)
በክልሉ የተጀመሩ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የድጋፍና ክትትል ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ ገለጹ
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ