ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሽብርተኛው አይኤስ አይኤስ ቡድን ለማሸነፍ የተቋቋመው ዓለም አቀፍ ጥምረት የሚኒስትሮች ስብስባ ላይ እየተሳተፉ ነው
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የአይኤስ አይኤስ የሽብር ቡድን ለማሸነፍ የተቋቋመው ዓለም አቀፍ ጥምረት በሳዑዲ አረቢያ ጅዳ እያካሄደ በሚገኘው የሚኒስትሮች ስብስባ ላይ እየተሳተፉ ነው።
ለአንድ ቀን በሚቆየው ስብሰባ የጥምረቱ አባል አገራት የሽብርተኛ ቡድኑን በሁሉም አቅጣጫዎች ለማሸነፍ የሚያስችሉ እርምጃዎችን ለመውሰድ ዳግም ቁርጠኝነታቸውን ያረጋግጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከስብስባው ጎን ለጎን የሁለትዮሽ ውይይቶችን እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 25 ሺህ 338 ሊትር ቤንዝልና 62 ሺ 686 ሊትር ናፍጣ በቁጥጥር ስር መዋሉን የክልሉ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ አስታወቀ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፍትህና የጸጥታ ዘርፍ አመራሮችና ባለሙያዎች ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ
ከአየር ንብረት ተፅዕኖ ጋር እየተስተዋሉ ያሉትን ችግሮች ለመከላከል ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን አስታወቀ