ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሽብርተኛው አይኤስ አይኤስ ቡድን ለማሸነፍ የተቋቋመው ዓለም አቀፍ ጥምረት የሚኒስትሮች ስብስባ ላይ እየተሳተፉ ነው
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የአይኤስ አይኤስ የሽብር ቡድን ለማሸነፍ የተቋቋመው ዓለም አቀፍ ጥምረት በሳዑዲ አረቢያ ጅዳ እያካሄደ በሚገኘው የሚኒስትሮች ስብስባ ላይ እየተሳተፉ ነው።
ለአንድ ቀን በሚቆየው ስብሰባ የጥምረቱ አባል አገራት የሽብርተኛ ቡድኑን በሁሉም አቅጣጫዎች ለማሸነፍ የሚያስችሉ እርምጃዎችን ለመውሰድ ዳግም ቁርጠኝነታቸውን ያረጋግጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከስብስባው ጎን ለጎን የሁለትዮሽ ውይይቶችን እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

More Stories
ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በርስ ግንኙነትና አንድነትን የሚያጠናክር ተግባር መሆኑ ተገለጸ
በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል አለባቸዉ – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ
የሕዝባችንን የልማት ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ የመመለስና ሜጋ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት የማጠናቀቅ ቁርጠኝነታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)