ኮሚሽኑ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ወክለው ለሚሳተፉ ተወካዮች ያዘጋጀው መድረክ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ: ሰኔ 01/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ወክለው ለሚሳተፉ ተወካዮች ያዘጋጀው መድረክ በሀዋሳ ከተማ ሚሊንየም አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል::
በችግሮቻቸው ዙሪያ ያልተመካከሩ ሀገራት ዛሬ በቀውስ ውስጥ እንደሚገኙ የተናገሩት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ አዳዬ ናቸው::
ለዘመናት ሲንከባለሉ በመጡ በርካታ ጉዳዮች ጊዜ ሰጥተን ባለመመካከራችን አሁን ለሚስተዋለው አለመግባባቶች ምክንያት ሆነዋል ያሉት ኮሚሽነሩ አሁን ግን በውይይት ለችግሮቻችን መፍትሔ የምናበጅበት ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል::
የምክክር ሂደቱ ሁሉንም ያሳተፈ ሲሆን የሀይማኖት እና የባህል አባቶች፣ የፖለቲካ መሪዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ከስሜት በፀዳ መንገድና ኢትዮጵያን በሚያሻግር መልኩ ሰፊ ምክክር ያደርጋሉ ብለዋል::
በዛሬው እለት ኮሚሽኑ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ወክለው ለሚሳተፉ ተወካዮች ባዘጋጀው መድረክ ላይ 3 ተወካዮች የሚመረጡ ይሆናል:: ከሚመረጡ ተወካዮች መካከል 2ቱ ዋና ተሳታፊ የሚሆኑ ሲሆን አንድ ሰው ደግሞ ተጠባባቂ ይሆናል ተብሏል::
ተወካዮቹ የሚመረጡት ለእውነት ባላቸው አቋም፣ በእውቀት፣ በማህበረሰብ ዘንድ ባላቸው ተአማኒነት ላይ ተመስርቶ ይሆናልም ነው ያሉት ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ::
በሀዋሳ ከተማ በሁለት ማዕከላት ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የተውጣጡ 3 ሺ 600 ዜጎች በውይይት መድረኩ እየተሳተፉ ይገኛሉ::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ
More Stories
የሸኮ ከተማ አስተዳደር በመደራጀቱ የተለያዩ መንግስታዊ አገለግሎቶችን በአቅራቢያ ማገኘታቸው እንዳስደሰታቸው የከተማው ነዋሪዎች ገለፁ
በተለያየ ዘርፍ በማህበር በመደራጀት ተጠቃሚ መሆናቸውን በሐመር ወረዳ በማህበር የተደራጁ ወጣቶች ተናገሩ
የጎፋ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ በዞኑ ለሚገኙ 50 አካል ጉዳተኞች 3 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የሚገመት የዊልቸር ድጋፍ አደረገ