ኮሚሽኑ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ወክለው ለሚሳተፉ ተወካዮች ያዘጋጀው መድረክ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል
ሀዋሳ: ሰኔ 01/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ወክለው ለሚሳተፉ ተወካዮች ያዘጋጀው መድረክ በሀዋሳ ከተማ ሚሊንየም አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል::
በችግሮቻቸው ዙሪያ ያልተመካከሩ ሀገራት ዛሬ በቀውስ ውስጥ እንደሚገኙ የተናገሩት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ አዳዬ ናቸው::
ለዘመናት ሲንከባለሉ በመጡ በርካታ ጉዳዮች ጊዜ ሰጥተን ባለመመካከራችን አሁን ለሚስተዋለው አለመግባባቶች ምክንያት ሆነዋል ያሉት ኮሚሽነሩ አሁን ግን በውይይት ለችግሮቻችን መፍትሔ የምናበጅበት ዕድል ተፈጥሯል ብለዋል::
የምክክር ሂደቱ ሁሉንም ያሳተፈ ሲሆን የሀይማኖት እና የባህል አባቶች፣ የፖለቲካ መሪዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በሀገራቸው ጉዳይ ላይ ከስሜት በፀዳ መንገድና ኢትዮጵያን በሚያሻግር መልኩ ሰፊ ምክክር ያደርጋሉ ብለዋል::
በዛሬው እለት ኮሚሽኑ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ወክለው ለሚሳተፉ ተወካዮች ባዘጋጀው መድረክ ላይ 3 ተወካዮች የሚመረጡ ይሆናል:: ከሚመረጡ ተወካዮች መካከል 2ቱ ዋና ተሳታፊ የሚሆኑ ሲሆን አንድ ሰው ደግሞ ተጠባባቂ ይሆናል ተብሏል::
ተወካዮቹ የሚመረጡት ለእውነት ባላቸው አቋም፣ በእውቀት፣ በማህበረሰብ ዘንድ ባላቸው ተአማኒነት ላይ ተመስርቶ ይሆናልም ነው ያሉት ኮሚሽነር ዶ/ር ዮናስ::
በሀዋሳ ከተማ በሁለት ማዕከላት ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የተውጣጡ 3 ሺ 600 ዜጎች በውይይት መድረኩ እየተሳተፉ ይገኛሉ::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ
More Stories
በቅርቡ በሚሰጠው የ6ኛ እና የ8ኛ ክልላዊ ፈተና ላይ ከ53 ሺህ በላይ ተማሪዎች ለፈተና እንደሚቀርቡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሀዲያ ዞን ትምህርት መመሪያ አስታወቀ
“የብልጽግና ጉዞአችንና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ክልላዊ የንግዱ ማሕበረሰብ ማጠቃለያ የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ እየተካሄደ ነው
በዞኑ ኩረጃን የሚፀየፍ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ