የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ለ15ኛ ዙር በመደበኛና በተከታታይ የትምህርት ፕሮግራሞች በመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 255 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው
ከተመራቂ ተማሪዎች መካከል 276 ሴቶች መሆናቸው ተጠቁሟል።
የምረቃ ፕሮግራሙ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፈቃዱ፣ የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ አባል አቶ ማቲዎስ አኒዮ፣ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዳዊት ሃዬሶ እና የዩኒቨርስቲው ማኔጅመንት አባላት በተገኙበት እየተካሄ ይገኛል።
ዘጋቢ: ሳሙኤል መንታሞ – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
በክልሉ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሁለንተናዊ የልማት ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ
የእናቶችንና ጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ በሚደረጉ ጥረቶች ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለፀ
የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳደር (ዶ/ር ) እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ምርቃትና የመሰረተ ድንጋይ የማስቀመጥ ስነ-ስረዓት እየተካሄደ ይገኛል