መንግስት ተጠያቂነትን እና የሽግግር ፍትኅን ለማስፈን እየሠራ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በድጋሚ አረጋገጡ፡፡
አቶ ደመቀ መኮንን ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ ጋር ተወያይተዋል።
በዚህ ወቅትም ተጠያቂነትን እና የሽግግር ፍትኅን ለማረጋገጥ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች የሚመራ የጋራ ግብረ ኃይል እንደተቋቋመ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡
የሽግግር ፍትኅን ለማስፈን መተባበር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይም ከኮሚሽነሩ ጋር መክረዋል፡፡
ከፍተኛ ኮሚሽነሩ ለፕሪቶሪያ የሠላም ስምምነት ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ÷ ፅሕፈት ቤታቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
ሠላምን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረትም ፅሕፈት ቤታቸው እንደሚደግፍ አስምረውበታል።
More Stories
በተቋማትና በባለሙያዎች መካከል የውድድር መንፈስ በመፍጠር ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቀቤና ልዩ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌዴኦ ዞን በ2017 ዓ.ም በመኸር እርሻ ከ24 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን አቅዶ እየሠራ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ
”የምንተክላቸው ችግኞች ለትውልድ ተሻጋሪ ትሩፋትን የሚያስገኙ ናቸው” – ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ