መንግስት ተጠያቂነትን እና የሽግግር ፍትኅን ለማስፈን እየሠራ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በድጋሚ አረጋገጡ፡፡
አቶ ደመቀ መኮንን ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ ጋር ተወያይተዋል።
በዚህ ወቅትም ተጠያቂነትን እና የሽግግር ፍትኅን ለማረጋገጥ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች የሚመራ የጋራ ግብረ ኃይል እንደተቋቋመ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡
የሽግግር ፍትኅን ለማስፈን መተባበር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይም ከኮሚሽነሩ ጋር መክረዋል፡፡
ከፍተኛ ኮሚሽነሩ ለፕሪቶሪያ የሠላም ስምምነት ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ÷ ፅሕፈት ቤታቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
ሠላምን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረትም ፅሕፈት ቤታቸው እንደሚደግፍ አስምረውበታል።

More Stories
በከምባታ ዞን ሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርአት (E-LMIS) ምዝገባ በይፋ መጀመሩን የከተማው ኢንተርፕራይዝና ሥራ ዕድል ፈጠራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም በተከሰተው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ተደረገ
ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ጨምሮ ለእሳት አደጋ መንስኤ የሚሆኑ የመጠቀሚያ ዕቃዎችን በጥንቃቄ በመጠቀም በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ