መንግስት ተጠያቂነትን እና የሽግግር ፍትኅን ለማስፈን እየሠራ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በድጋሚ አረጋገጡ፡፡
አቶ ደመቀ መኮንን ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ ጋር ተወያይተዋል።
በዚህ ወቅትም ተጠያቂነትን እና የሽግግር ፍትኅን ለማረጋገጥ በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች የሚመራ የጋራ ግብረ ኃይል እንደተቋቋመ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል፡፡
የሽግግር ፍትኅን ለማስፈን መተባበር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይም ከኮሚሽነሩ ጋር መክረዋል፡፡
ከፍተኛ ኮሚሽነሩ ለፕሪቶሪያ የሠላም ስምምነት ያላቸውን አድናቆት ገልጸው ÷ ፅሕፈት ቤታቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
ሠላምን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረትም ፅሕፈት ቤታቸው እንደሚደግፍ አስምረውበታል።

More Stories
በህዝባዊ አንድነት የተጀመሩት የልማት ስራዎች ቀጣይነት እንዲኖረው ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል
በዞኑ የሚገኙ የተፈጥሮ ፀጋዎችና እምቅ ባህሎችን በማልማት ሀገሪቱ የጀመረችውን የቱሪዝም ሪፎርም እውን ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ
በኮንሶ ማህበረሰብ ዘንድ ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር የሚደረግበት “ኼልታ” ባህላዊ የአስተዳደር ሥርዓት ዓለም አቀፍ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ እንደሚሰራ ተገለጸ