ሀዋሳ፡ መሰከረም 09/2019 ዓ.ም (ደሬቴድ) የወላይታ ብሄር የባህል፣ የታሪክና የቋንቋ ሲምፖዚየም በጉተራ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ሲምፖዚየሙ የወላይታ ብሔር የዘመን መለወጫ የጊፋታ በዓል በሚከበርበት ዋዜማ ላይ የሚካሄድ ነው።
የባህልና የቋንቋ ሲምፖዚየም መድረክ የተለያዩ የወላይታ ባህላዊ ጭፈራና ሀያ ሌኬ ጫዋታ እና በሲምፖዚየሙ ጥናታዊ ፅሑፍ ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
በመድረኩ የፌደራል፣ የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ ከወረዳና ከተማ አስተዳደር የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዘጋቢ፡ ፈቃዱ ማትዮስ – ከዋካ ጣቢያችን

More Stories
የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ፍትሀዊ በሆነ መልኩ ተደራሽ ለማድረግና በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ድጋፍ ወሳኝ ነው – አቶ መዝረዲን ሁሴን
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያና የቀጣይ አምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የሚመክር ጉባኤ በሆሳዕና ከተማ እያካሄደ ነው
ታላቁ የጊፋታ ዋዜማ የሩጫ ውድድር በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሄደ