የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት 32ኛ የምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም እያካሄደ ነው
ፎረሙ ባለፈው ዓመት በጥንካሬ እና በድክመት የተለዩ ጉዳዮችን በመፈተሽ ድክመቶችን ለማረም እና በጠንካራ ጎን የተለዩ ጉዳዮችን ለማስቀጠል የተዘጋጀ መሆኑ ተመላክቷል።
በፎረሙ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዞኑ ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ አቶ ፀጋዬ ታደሰ÷ ፎረሙ ሁሉም በዞኑ ሥር በሚገኙ መዋቅሮች የሚገኙ ምክር ቤቶች ልምድ ልውውጥ የሚያደርግበት መሆኑን ተናግረዋል።
አክለውም በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ምክር ቤቶችን ከማብቃት አንጻር የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠታቸውን ጠቁመዋል።
ለምክር ቤቱ በተሰጠው ስልጣን መነሻ ህግ ማውጣት እና የሚወጡ ህጎች ተፈጻሚነትን በመከታተል የአስፈጻሚ አካላት የክትትል እና ድጋፍ ሥራ በቋሚ ኮሚቴ አማካኝነት መሠራቱን አመላክተዋል።
የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ(ዶ/ር) በበኩላቸው÷ ባለፈው አንድ ዓመት ምክር ቤቱ ህግ ከማውጣት ባሻገር የወጡ ህጎች ተፈጻሚነት፣ በዓመቱ የጸደቁ ዕቅዶች ምን ያህል ተግባራዊ መደረጋቸውን እና የህዝብ እርካታ ምን እንደሚመስል በተለያዩ መንገዶች ሲገመግም ቆይቷል ብለዋል።
በተለይ የምክር ቤት አባላት የህዝብ ተወካዮች እንደመሆናቸው ህዝቡ የሚያነሳቸውን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ እየሠሩ ያለውን ሥራ አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በፎረሙ የዞኑ ካቢኔዎች፣ የዞኑ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች፣ የሶስቱም ዘርፍ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች፣ የወረዳና ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በፎረሙ በ2018 በጀት ዓመት ከቀበሌ ጀምሮ የህዝብ ምክር ቤቶች ያከናወኑት ተግባራት በሪፖርት ቀርቦ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።
ዘጋቢ: እንግዳየሁ ቆሳ- ከይርጋጨፌ ጣቢያችን
የጌዴኦ ዞን ምክር ቤት 32ኛ የምክር ቤቶች የጋራ ምክክር ፎረም እያካሄደ ነው

More Stories
የላስካ ከተማ ነዋሪዎችን የመሠረተ ልማት ጥያቄ ለመመለስ እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ
የፈጠራ ስራ አዳዲስ ሀሳቦችንና እውቀቶችን በተግባር ላይ በማዋል ወደሚጨበጥ ኢኮኖሚ ለመቀየር ፋይዳው የጎላ መሆኑን በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
ለስድስት ሺህ ተማሪዎች ከ9 ሚሊየን ብር በላይ በማውጣት ድጋፍ ተደርጓል – የከምባታ ልማት ማህበር