‎በትምህርት ጥራት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ከጅምሩ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ ተጠቆመ

‎በትምህርት ጥራት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ከጅምሩ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ ተጠቆመ

‎ይህ የተገለፀው የ2019 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር በይፋ በተጀመረበት ወቅት ነው።

‎የመማር ማስተማር መርሃግብሩን ያስጀመሩት የይርጋጨፌ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ብዙአየሁ ታደሰ፤ በትምህርት ጥራት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ከጅምሩ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አሳስበዋል።

‎የትምህርትን ስብራት ለመጠገን እንደሀገር የተያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ መምህራን፣ ወላጆች፣ ተማሪውና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ሚጠበቅባቸውን ለመወጣት ከወዲው መዘጋጀት እንዳለባቸው አስታውቀዋል።

‎በከተማው የሚገኙ ትምህርት ቤቶች በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የመማር ማስተማር ሥራቸውን በአግባቡ መጀመራቸውን ተዘዋውረው መመልከታቸውን የጠቀሱት አቶ ብዙአየሁ፤ በስነ-ምግባር የታነፀ፣ ስለ ሀገር ፍቅርና ብሔራዊ ጥቅም በተገቢው መንገድ የሚረዳ ትውልድ ለማፍራት በአፅንኦት ሊሰራ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

‎በይርጋጨፌ ከተማ የሚገኙ የመንግሥትና የግል ትምህርት ቤቶች የዛሬው ዕለት የመማር ማስተማር ተግባር አጀማመር ሂደታቸው በዞኑና በከተማው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የመስክ ምልከታ ተካሂዶባቸዋል።

‎ዘጋቢ፡ ሳሙኤል በቀለ – ከይርጋጨፌ ጣቢያችን