በዞኑ የቱሪስት ፍሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የኮንሶ ዞን ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ‎

በዞኑ የቱሪስት ፍሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የኮንሶ ዞን ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ

‎በ2018 በጀት አመት ከ3 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጪ ጎብኚዎች ዞኑን የጎበኙ ሲሆን ከ 4 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱ ተመላክቷል።

‎የኮንሶ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ዝናቡ ገሠሠ በ2018 በጀት አመት 438 የሀገር ውስጥና 2 ሺህ 851 የውጭ ሀገር ጎብኝዎች ዞኑን የጎበኙ ሲሆን ከዚህም 4 ሚሊየን 550 ሺህ ብር መገኘቱን አስታውቀዋል።

ከ2017 በጀት አመት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ የጎብኚ ቁጥር የጨመረ እና አፈፃፀሙም 168 በመቶ የገቢ ብልጫ እንዳለው አመላክቷል።

‎በሀገር ደረጃ የተደረገው የፖሊሲ ለውጥ፣ የዞኑ ሰላም መሆን አልፎም ቱሪዝሙን ወደ ፊት የማምጣቱ ተግባር ትልቅ መነቃቃት በመፍጠሩ የቱሪስቱንና የገቢ አቅም እንዲጨምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አቶ ዝናቡ ገልጸዋል።

‎በቀጣይ የጎብኚዎችን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ መዳረሻዎቹን ምቹና ሳቢ እንዲሆኑ፣ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲኖር ከማድረግ ባሻገር ማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝምን ለማሳደግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት አዳዲስ ስትራቴጂዎች መቀረጻቸው ተጠቁሟል።

‎በሀገራችን የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎች ከሀገር አልፎ ለዓለም በይበልጥ ለማስተዋወቅ የሁሉም ድርሻ የጎላ በመሆኑ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ የመምሪያው ኃላፊ አጽንኦት ሰጥተዋል።

‎ዘጋቢ: ተዋበች ዳዲ – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን