በዞኑ የቱሪስት ፍሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የኮንሶ ዞን ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ
በ2018 በጀት አመት ከ3 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጪ ጎብኚዎች ዞኑን የጎበኙ ሲሆን ከ 4 ሚሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱ ተመላክቷል።
የኮንሶ ዞን ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ዝናቡ ገሠሠ በ2018 በጀት አመት 438 የሀገር ውስጥና 2 ሺህ 851 የውጭ ሀገር ጎብኝዎች ዞኑን የጎበኙ ሲሆን ከዚህም 4 ሚሊየን 550 ሺህ ብር መገኘቱን አስታውቀዋል።
ከ2017 በጀት አመት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ የጎብኚ ቁጥር የጨመረ እና አፈፃፀሙም 168 በመቶ የገቢ ብልጫ እንዳለው አመላክቷል።
በሀገር ደረጃ የተደረገው የፖሊሲ ለውጥ፣ የዞኑ ሰላም መሆን አልፎም ቱሪዝሙን ወደ ፊት የማምጣቱ ተግባር ትልቅ መነቃቃት በመፍጠሩ የቱሪስቱንና የገቢ አቅም እንዲጨምር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አቶ ዝናቡ ገልጸዋል።
በቀጣይ የጎብኚዎችን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ መዳረሻዎቹን ምቹና ሳቢ እንዲሆኑ፣ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲኖር ከማድረግ ባሻገር ማህበረሰብ አቀፍ ቱሪዝምን ለማሳደግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት አዳዲስ ስትራቴጂዎች መቀረጻቸው ተጠቁሟል።
በሀገራችን የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎች ከሀገር አልፎ ለዓለም በይበልጥ ለማስተዋወቅ የሁሉም ድርሻ የጎላ በመሆኑ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ የመምሪያው ኃላፊ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ዘጋቢ: ተዋበች ዳዲ – ከአርባ ምንጭ ጣቢያችን
በዞኑ የቱሪስት ፍሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የኮንሶ ዞን ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ

More Stories
በበጎ ተግባራት ላይ መንግስት ከሚያደርገው ጥረት ጎን ለጎን መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ሲቪክ ማህበራት ድርሻ የጎላ መሆኑ ተገለጸ
ለኤልኒኖ የማይበገር ግብርናን መገንባትና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የእንስሳት ጤና ጥበቃ፣ የዝርያ ማሻሻልና የሌማት ትሩፋት ሥራዎች ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባ ተገለጸ
የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት በማጠናከር ክልላዊ አንድነትን ማጎልበት እንደሚገባ ተገለጸ