የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ብሔረሰቦች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን በቴፒ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።

በዚሁ መደበኛ ጉባኤ ላይ ምክር ቤቱ 4ኛ አመት 6ኛ መደበኛ ጉባኤ ቃለ ጉባኤን መርምሮ በማፅደቅ የ2018 የብሔረሰቦች ምክር ቤት ዕቅድ አፈፃፀም ላይ ውይይት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

በተጨማሪም የምክር ቤቱ የ2019 በጀት ዓመት ጠቋሚ ዕቅድ ቀሪቦ ውይይት ተደርጎበት እንደሚፀድቅም ከወጣው መርሃ ግብር መረዳት ተችሏል።

በጉባኤው ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የምክር ቤቱ አባላት በመሳተፍ ላይ ናቸው።

ዘጋቢ: በዛብህ ታደሰ – ከማሻ ጣቢያችን