ለሀገራችን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ስኬታማነት ሁሉም የራሱን አስተዋጽኦ ማበርከት አለበት – ኃይለየሱስ ታዬ

ለሀገራችን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ስኬታማነት ሁሉም የራሱን አስተዋጽኦ ማበርከት አለበት – ኃይለየሱስ ታዬ

ሀዋሳ፡ ሰኔ 22/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ለሀገራችን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ስኬታማነት ሁሉም የራሱን አስተዋጽኦ ማበርከት እንዳለበት የህገ መንግስትና ፌደራልዝም አስተምህሮ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኃይለየሱስ ታዬ ገለጹ።

ለደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ለዋናው እና ለቅርንጫፍ ጣቢያዎች አመራሮችና ጋዜጠኞች የአሠልጣኞች ስልጠና አካል የሆነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሀ-ግብር በሀዋሳ ከተማ ታቦር ተራራ ላይ ተካሂዷል።

በዚህ መርሀ-ግብር ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የህገ መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኃይለየሱስ፤ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ ጥቅሙ የትየለሌ ስለሆነ ሌሎችም ተመሣሣይ ተግባር እንዲፈጽሙ ጥሪ አቅርበዋል።

የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘላለም ገነሞ በበኩላቸው፤ የችግኝ ተከላ መርሀ-ግብሩ ከህገ መንግስትና ፌደራሊዝም አስተምህሮ ማዕከል ጋር በጋራ የተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው የጥላና የፍራፍሬ ችግኞች በታቦር ተራራ ላይ መትከል መቻሉን ጠቁመዋል።

አክለውም ማዕከሉ ከደሬቴድ ጋር በዚህና በሌሎች የአስተምህሮ መርሀ-ግብሮች እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

በመርሀ-ግብሩ የማዕከሉ፣ የደሬቴድ እና የቅርንጫፍ ጣቢያ አመራሮችና ጋዜጠኞች ተሳትፈዋል።

ዘጋቢ፡ ታሪኳ በቀለ