የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ

በቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወ/ሮ ልክነሽ ስርገማ የተመራው የቅኝት ቡድን በቁሊቶ ከተማ በተለያዩ ተቋማት እየለሙ ያሉ የግብርና ስራዎችን ተመልክቷል።

በቁሊቶ ከተማ ዕድገት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የቁሊቶ ማረሚያ ተቋም፣ የስላሴና ማርያም ቤተክርስቲያኞች ውስጥ እየለሙ ያሉ የግብርና ስራዎች ምልከታ ተደርጎባቸዋል።

በተቋማቱ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የቡና ምርት በወጉ እየተሰራበት መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ተመልክቷል።

በከተማው የሚገኙ ሁሉም ተቋማት የግብርና ስራዎችን እያለሙ ሲሆን በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረውን ውጥን ዳር ለማድረስ አጋዥ ናቸው ተብሏል።

ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ