የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርናና ገጠር ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ የግብርና ስራዎችን ተመለከተ
በቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወ/ሮ ልክነሽ ስርገማ የተመራው የቅኝት ቡድን በቁሊቶ ከተማ በተለያዩ ተቋማት እየለሙ ያሉ የግብርና ስራዎችን ተመልክቷል።
በቁሊቶ ከተማ ዕድገት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የቁሊቶ ማረሚያ ተቋም፣ የስላሴና ማርያም ቤተክርስቲያኞች ውስጥ እየለሙ ያሉ የግብርና ስራዎች ምልከታ ተደርጎባቸዋል።
በተቋማቱ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የቡና ምርት በወጉ እየተሰራበት መሆኑን ቋሚ ኮሚቴው ተመልክቷል።
በከተማው የሚገኙ ሁሉም ተቋማት የግብርና ስራዎችን እያለሙ ሲሆን በምግብ ራስን ለመቻል የተጀመረውን ውጥን ዳር ለማድረስ አጋዥ ናቸው ተብሏል።
ዘጋቢ: ባዬ በልስቲ

More Stories
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለአካባቢው ማህበረሰብ ለውጥ የሚበጅ፤ ዘመኑን በሚዋጅ የቴክኖሎጂ እውቀት የበለጸጉ ዜጎች የሚፈልቁበት ተቋም ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የኢፌዲሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ
የሴቶችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ የሚገድቡ እንቅፋቶችን በትብብር መፍታት እንደሚገባ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድናስር ገለጹ
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ39ኛ ዙር የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በደመቀ ሁኔታ እያካሄደ ይገኛል