የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለ6ኛ ዙር በተለያዮ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በደማቅ ስነ-ስርአት በማስመረቅ ላይ ይገኛል
በዛሬው ዕለት ለመጀመሪያ ጊዜ በመመረቅ ለይ የሚገኙት የእንስሳት ህክምና ተማሪዎችን ጨምሮ ለሶስተኛ ጊዜ የሚያስመርቃቸው የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች፣ የህክምና ሳይንስ ኮሌጅ እና የህግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች መሆናቸው ተገልጿል።
በምረቃ ስነ-ስርአቱ ላይ የክብር እንግዳ የሆኑት የኢፌዲሪ የፌደሬሽን ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤና የጂንካ ዩኒበርሲቲ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አገኘሁ ተሻገርን ጨምሮ የዩኒበርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ ይትባረክ የዩኒበርሲቲው የቦርድ አባላት፣ ሌሎች የስራ ኃላፊዎችና የፌደራል፣ የክልልና የዞን ልዩ ልዩ አመራሮች፣ ተመራቂ ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ታድመዋል፡፡
ዘጋ፡ ተመስገን ሰይፉ – ከጂንካ ጣቢያችን

More Stories
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ39ኛ ዙር የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በደመቀ ሁኔታ እያካሄደ ይገኛል
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና በተከታታይ ትምህርት መርሃ ግብር በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ ድግሪ እና በስፔሻሊቲ ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 479 ተማሪዎችን በዋናው ግቢ እያስመረቀ ነው
በመጪው የትምህርት ዘመን የጉራጊኛ ቋንቋ የ4ኛ ክፍል የሙከራ ትምህርት ለማስጀመር የመጽሀፍ ዝግጅት መጠናቀቁን የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ