የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛና በተከታታይ ትምህርት መርሃ ግብር በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ ድግሪ እና በስፔሻሊቲ ያሰለጠናቸውን 1 ሺህ 479 ተማሪዎችን በዋናው ግቢ እያስመረቀ ነው
ከዩኒቨርሲቲው የ17ኛው ዙር ጠቅላላ ተመራቂ ተማሪዎች መከከል 539 ሴቶች ሲሆኑ 940 ደግሞ ወንዶች መሆናቸው ተመላክቷል።
ከዕለቱ ተመራቂዎች መካከል 45 የሕክምና ዶክተሮች እና 15 ስፔሻሊስት ሐኪሞች መሆናቸውን ከዩኒቨርሲቲው የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ አባል እና የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማቲዎስ አኒዮ፣ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዳዊት ሃዬሶ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የተመራቂ ተማሪዎች ቤተሰቦችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።
ዘጋቢ: ሙጂብ ጁሃር – ከሆሳዕና ጣቢያችን

More Stories
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ39ኛ ዙር የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በደመቀ ሁኔታ እያካሄደ ይገኛል
የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ለ6ኛ ዙር በተለያዮ ፕሮግራሞች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በደማቅ ስነ-ስርአት በማስመረቅ ላይ ይገኛል
በመጪው የትምህርት ዘመን የጉራጊኛ ቋንቋ የ4ኛ ክፍል የሙከራ ትምህርት ለማስጀመር የመጽሀፍ ዝግጅት መጠናቀቁን የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ