የአረንጓዴ አሻራ ልማት ኢትዮጵያ ገፅታዋን የቀየረችበትና የአየር ንብረቷ እንዲስተካከል ያደረገ አመረቂ ተግባር መሆኑ ተገለፀ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 07/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የአረንጓዴ አሻራ ልማት ኢትዮጵያ ገፅታዋን የቀየረችበትና የአየር ንብረቷ እንዲስተካከል ያደረገ አመረቂ ተግባር መሆኑ ተገልጿል፡፡
የፌደራል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በቤንች ሸኮ ዞን የተለያዩ የልማት ሥራዎችን መጎብኘታቸው ከፍተኛ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸው የዞኑ አመራሮችና ጎብኝት የተደረገላቸው አካላት ገልፀዋል።
ክልሎችና የአካባቢው መስተዳድሮች የአካባቢን ፀጋ ተጠቅሞ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ዜጎች የኑሮ ውድነት ጫናን ለመቀነስ እየተሰራ ያለውን ተግባራት በቤንች ሸኮ ዞን በተደረገው ጉብኝት መመልከታቸውን የኢፌደሪ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር አለሙ ስሜ ተናገረዋል።
በዚህም የአረንጓዴ አሻራው ልማት ኢትዮጵያ በዓለም ገፅታዋን የቀየረችበትና የአየር ንብረቷ እንዲስተካከል ያደረገችበት አመረቂ ሥራ የተከናወነበት ተግባር እንደሆነም ገልፀዋል።
ከሰሞኑ ሀገር አቀፍ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት በቤንች ሸኮ ዞን የፌደራል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ያደረጉት ጉብኝት ለአመራሩም ሆነ ለአርሶ አደሩ ከፍተኛ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸውም አመላክተዋል።
የዞኑ የብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዮናስ ኬና፣ የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ጉብላ እና የጉራፈረዳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ስንታየሁ ካረካ በሰጡት አስተያየት ጉብኝቱ ለቀጣዩ ሥራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከተላቸው ተናገረዋል።
ለክልሉ 2ሺህ ኩንታል ሾኔ በቆሎ እና 7 መቶ ኩንታል ሩዝ ምርጥ ዘር ማሰረከባቸውን አቶ ገመቹ ደግፌ የኩጃ ዘር ብዜት እርሻ ኃላፊ የገለፀ ሲሆን የሴካ አግሮ ፕሮሰሲንግ ኃላፊነት የተወሰነ የግል ማህበርም የተቀናጀ ግብርናን እያከናወነ ከመሆኑም ባለፈ በፌደራል ሚነስቴር መስሪያ ቤት መጎበኘታቸው እንዳስደሰታቸው ተናገረዋል።
የአረንጓዴ አሻራ፣ የሌማት ትሩፋቶች፣ የክረምት በጎ ሥራ እንዲሁም የኤክስፖርት ምርቶች ተጎብኝተዋል።
ዘጋቢ፡ አብዲሳ ዮናስ – ከሚዛን ጣቢያችን

More Stories
“አንድነት የሚገነባው በውይይት ነው፤ ሰላም የሚጠናከረው በመግባባት ነው” ኢማም ሐጂ አብዱልሃዲ ሼክ አህመድ ቡርሃን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት
መደበኛ ባልሆነ መልኩ የሎተሪ ዕድል ሙከራን “ዕቁብ” በሚል ሽፋን በህገ-ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍትህ ጽ/ቤት አሳሰበ
መንግስት ባለፉት ጊዜያት በስርዓተ ትምህርት እና በመማር ማስተማር ሂደት የነበረውን ክፍተት ለመሙላት እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራ በመስራት መደገፍ እንደአለባቸው ተገለጸ