‎በኮሬ ዞን ምክር ቤት 18ኛው የሰንደቅዓላማ ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

‎በኮሬ ዞን ምክር ቤት 18ኛው የሰንደቅዓላማ ቀን በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

‎ሀዋሳ፡ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም (ደሬቴድ) ዕለቱ “ሰንደቅዓላማችን ለኢትዮጵያ የከፍታ ዘመን ብስራት ፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ህዳሴ” በሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡

‎ስርዓቱን በንግግር የከፈቱት የኮሬ ዞን ዋና አፈጉባዔ ወይዘሮ አካላት በቀለ፥ የእንኳን አደረሰን መልዕክት በማስተላለፍ የኢትዮጵያ ስንደቅዓላማ የሚከበረው ለሀገሪቱ ሉኣላዊት መስዋዕትነት የከፈሉትን በማስታወስ ነው ብለዋል።

‎አክለውም የባዲራ ስነ-ስርዓት ሁሌም በማሰብ እንደየሁኔታው ሰዓታት የተለያዩ ቢሆንም ሁሉንም በተገቢ ጥንቃቄ ማውጣትና ማውረድ እንደሚጠበቅም አስታውሰዋል።

‎ከስነ-ስርዓቱ ተካፋዮች መካከል ወይዘሮ ፍሬህይወት ቢተው እና አቶ አስረስ ዘውዴ ስንደቅዓላማ የሀገር ሉአላዊነት መገለጫ መሆኑን በመግለጽ፥ ዕለቱን ጠብቆ ማክበር ብቻ ሳይሆን ለልጆቻቸውም እንደሚያስተምሩ ተናግረዋል።

‎የባንዲራ ቀን አከባበር ስነ-ስርዓት ላይ ስለ ሀገር አንድነት እና ልማት በኮሬ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ሙሉቀን በቀለ አማካኝነት የዕለቱ ተሳታፊዎች ቃለመሀላ ፈጽመዋል።


‎አዘጋጅ፡ ምርጫ መላኩ – ከይርጋ ጨፌ ጣቢያችን