በቡታጅራ ከተማ ቢሮዎች ዝግጁ ሆነዋል
ሀዋሳ: ጳጉሜ 03/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በቡታጅራ ከተማ የተመደቡ ክላስተር መሥሪያ ቤቶች የቢሮ ዝግጅት መደረጉን የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ገለፁ::
ጳጉሜ 04 ቀን 2015 ዓ.ም የሥራ ማስጀመሪያ መርሀግብር እንደሚከናወንም ተገልጿል::
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማዕከል ከተማ ከሆኑት አንዷ የሆነችው የቡታጅራ ከተማ አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅቶችን ማጠናቀቋን የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሀሰን ተናግረዋል::
ከደሬቴድ ጋር ቆይታ ያደረጉት ምክትል አስተዳዳሪው ከተማው የክላስተር ከተማ ሆና መመረጧ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ያሉት ነው ብለዋል:: ይህም ከሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ከገበያ ትስስር እና ከኢንቨስትመንት አንፃር ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል ነው ያሉት::
ከተማዋ ለእንግዶች ምቹ ትሆን ዘንድ ከከተማ ፅዳት ጀምሮ እስከ ቢሮ ዝግጅት ያሉ ተግባራት መከናወናቸውን አስታውቀዋል:: ይህን ተከትሎ ጳጉሜ 04 ቀን 2015 ዓ.ም ከፍተኛ የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ይፋዊ የሥራ ማስጀመሪያ መርሀግብር ይካሄዳል::
የቢሮ ኃላፊዎች በቀጥታ ወደ ሥራ በመግባት የተሰጣቸውን የህዝብና የመንግስታ ኃላፊነት ያለምንም ችግር ይወጡ ዘንድ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ሥራ መሠራቱን አቶ ሙስጠፋ ገልጸዋል::
ከከተማዋ ባለሀብቶች ጋር በመነጋገር ለኃላፊዎቹ ለ6 ወር በነፃ የሚኖሩበት የመኖሪያ ቤት ተዘጋጅቷል ብለዋል:: ባለሀብቱ ላሳየው በጎ ፈቃደኝነት ምስጋና አቅርበዋል::
ወደ ከተማዋ ተመድበው የሚመጡ የመንግስት ሠራተኞችም ባይተዋርነት ሳይሰማቸው እንደ ቤታቸው ሆነው እንዲኖሩ የሚያስችል ሥራ ከህብረተሰቡ ጋር ተሰርቷል ብለዋል::
እድገት በጊዜ ሂደት የሚመጣ መሆኑን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ ለእንግዶች በተመጣጣኝ ዋጋ የመኖሪያ ቤት ማከራየት መልካም መሆኑን አንስተዋል::
በአራቱ ቢሮዎች ተመድበው ወደ ከተማዋ ለሚመጡ የመንግስት ሠራተኞች በማህበር በማደራጀት የመኖሪያ ቤት እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑም ቅድሚያ ተሰጥቶ እንደሚሠራ አብራርተዋል::
ዘጋቢ: ማሬ ቃጦ
More Stories
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
ወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ የተሰኘው ግብረ-ሰናይ ድርጅት ከ136 ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎች ኑሮ እንዲሻሻል ማስቻሉን አስታወቀ
በበዓላት ወቅት በሚፈጸሙ የእርድ ስነ-ስርዓት ለቆዳና ሌጦ ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ተጠቆመ