የጋሞ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ አባይነህ አበራ በጋሞ ዞን ህዝብ ም/ቤት 4ኛ ዙር መርሀ ግብር 10ኛ አመት የስራ ዘመን 19ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር በዞኑ ያለውን አብሮነትና መቻቻል በማጠናከር ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።
በሰላምና ጸጥታ፣ ባህላዊ እሴቶችን ማጎልበት ይገባል ያሉት አቶ አባይነህ የዞኑን ሰላም በይበልጥ ለማረጋገጥ ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባልም ብለዋል።
እንደዞን ያለውን ውስን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በተቀናጀ አግባብ መመለስ እንደሚገባ ጠቅሰው እቅድን በተሳካ መልኩ ለመፈፀም በዞኑ ያሉ መዋቅሮች ሀላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንሚገባም አሳስበዋል።
በጉባኤው አቶ ሰብስቤ ቡናቤ የጋሞ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሀላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ፣ ወ/ሮ ልሳነ ወረቅ ካሳዬ የጋሞ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ሀላፊ፣ አቶ መኮንን ሞገስ የዞኑ ርእዮተ አለም ዘርፍ ሀላፊና የመንግስት ረዳት ተጠሪ፣ አቶ አብርሀም አርጋው የዞኑ ብልጽግና ፓርቲ የአጀረጃጀት ዘርፍ ሀላፊና የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሆነው እንዲሾሙ የቀረበውን ምክር ቤቱ ተቀብሎ አጽድቋል።
ጉባኤው በቀጣይም የጋሞ ዞን አስተዳደር የ2015 በጀት አመት አፈጻጸም ሪፖርትና የ2016 በጀት አመት እቅድ አንዲሁም የዞኑ ረቂቅ በጀት ቀርቦ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል።
ዘጋቢ፡ ማርታ ሙሉጌታ – ከአርባምንጭ ጣቢያችን
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለማየሁ ባውዲ በክልሉ የሚገኙ የየተለያዩ ብሔሮች ዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ !!
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አት ደመቀ መኮንን በመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ንግግር አደረጉ
300 ለሚሆኑ ወላጅ አጥ ተማሪዎች ኢትዮ- ቴሌኮም ሳውላ ድስትሪክት ከ270 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ