የሳውላ አዳሪ ትምህርት ቤት ግንባታ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ
በደቡብ ክልል በጎፋ ዞን ለሚገነባው የሳውላ አዳሪ ትምህርት ቤት የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ።
የመሠረት ድንጋዩን ያስቀመጡት የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ተጠሪ አቶ ተስፋዬ ቤልጅጌና ሌሎች የፌዴራልና የደቡብ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ስለመሆናቸው የኢዜአ መረጃ ያመለክታል።
ትምህርት ቤቱ በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማምጣት ያስችላሉ ተብለው ከተያዙ 50 አዳሪ ትምህርት ቤቶች አካል ሲሆን፣ ከትምህርት ቤቶቹ መካከል 5ቱ በደቡብ ክልል እንደሚገነቡ ታውቋል።
ትምህርት ቤቱ በአንድ ዓመት ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ በ2017 ዓ.ም የመማር ማስተማር ስራ ይጀመርበታል ተብሏል።
የትምህርት ቤቱን ግንባታ ወጪ ሰዎች ለሰዎች የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት እንደሚሸፍን ተገልጿል።
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለማየሁ ባውዲ በክልሉ የሚገኙ የየተለያዩ ብሔሮች ዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ !!
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አት ደመቀ መኮንን በመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ንግግር አደረጉ
300 ለሚሆኑ ወላጅ አጥ ተማሪዎች ኢትዮ- ቴሌኮም ሳውላ ድስትሪክት ከ270 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ