ውጤታማ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ ለማከናወን ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ ይገባል- የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ውጤታማ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ ለማከናወን ሁሉም የሚጠበቅበትን ሊወጣ እንደሚገባ የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር አሳሰበ፡፡
የዘንድሮውን የወጣቶች የክረም ወራት በጎ ፈቃድ አገለግሎት አስመልክተው የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዞኑ 2015 በጀት ዓመት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገለግሎት ለማከናወን የ2014 አፈፃፀም በመገመገም ወደ ተግባር መገባቱን የዞኑ ዋና አስተዳደር አቶ ቀበሌ መንገሻ አስታውቀዋል፡፡
በመርሀግብሩ ከ10 በላይ የሆኑ የተለያዩ ተግባራቶች ይከወናሉ ያሉት ኃላፊው የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ በትኩረት የሚሠራበት መሆኑን ዋና አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
አመራሩ ለተግባሩ ዕገዛ በማድረግ በኩል ከዞን ጀምሮ ከተሠራ በየዘርፉ እምርታዊ ለውጥን ማምጣት እንደሚቻል ገልጸዋል፡፡
ዘጋቢ፡ አብዲሳ ዮናስ- ከሚዛን ጣቢያችን
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለማየሁ ባውዲ በክልሉ የሚገኙ የየተለያዩ ብሔሮች ዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ !!
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አት ደመቀ መኮንን በመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ንግግር አደረጉ
300 ለሚሆኑ ወላጅ አጥ ተማሪዎች ኢትዮ- ቴሌኮም ሳውላ ድስትሪክት ከ270 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ