በጉራጌ ዞን ከ175 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ተመረቀ
ሀዋሳ፡ ሐምሌ 09/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጉራጌ ዞን እምድብር ከተማ ከ175 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በክልሉ መንግስት እና በ“ዋንወሽ” የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት የደቡብ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው በተገኙበት ተመርቋል።
የንጹህ መጠጥ ውሃው ከ35 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል።
የንጹህ መጠጥ ውሃ ተገንብቶ መጠናቀቅ የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሚናው የጎላ ነው።
በውሃ ምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የደቡብ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳውን ጨምሮ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ግርማ፣ የዞን ከፍተኛ አመራሮች፣ የከተማው አመራሮች፣ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡
ምንጭ ፡ የጉራጌ ዞን ኮሙኒኬሽን መምሪያ
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለማየሁ ባውዲ በክልሉ የሚገኙ የየተለያዩ ብሔሮች ዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ !!
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አት ደመቀ መኮንን በመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ንግግር አደረጉ
300 ለሚሆኑ ወላጅ አጥ ተማሪዎች ኢትዮ- ቴሌኮም ሳውላ ድስትሪክት ከ270 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ