በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለተከሰተው የምግብ እጥረት የሰብአዊ ድጋፍ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ተካሄደ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 22/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በመተባበር በደቡብ ኦሞ ዞን አራት ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለተከሰተው የምግብ እጥረት የሰብአዊ ድጋፍ የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አካሂዷል።
ድጋፍ የሚደረግላቸው ዳሰነች፣ ሐመር፣ ኛንጋቶም እና ሰላማጎ ወረዳዎች ሲሆኑ ድጋፉ ከ259 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነ በመርሃ-ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ተገልጿል።
ድጋፉ የአርብቶ አደሩን ማህበረሰብ ካለበት መሰረታዊ ችግር እንዲወጣ ለማድረግ ያለመ ስለመሆኑ ተጠቁሟል።
በሚደረገው የሰብዓዊ እርዳታ በአራቱም ወረዳዎች ከ140 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ታውቋል።
በመርሃ-ግብሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የአመራር አካላትን ጨምሮ የደቡብ ክልልና የዞኑ የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።
ዘጋቢ፡ ወንድወሰን ሽመል ከጂንካ ጣቢያችን
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለማየሁ ባውዲ በክልሉ የሚገኙ የየተለያዩ ብሔሮች ዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ !!
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አት ደመቀ መኮንን በመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ንግግር አደረጉ
300 ለሚሆኑ ወላጅ አጥ ተማሪዎች ኢትዮ- ቴሌኮም ሳውላ ድስትሪክት ከ270 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ