“በቤንች ሸኮ ዞን በጉራፈርዳ ወረዳ አሁን ላይ አንፃራዊ ሠላም በመገኘቱ የአካባቢው ማህበረሰብ ወደ ልማት መግባት ችሏል” ሲሉ የወረዳው ነዋሪዎች ተናገሩ
በዞኑ የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም ዘላቂ ለማድረግ በየደረጃው ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የቤንች ሸኮ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ አስታውቋል።
አቶ ዳዊት አሰፋና አቶ ባዬ አወቀ በቤንች ሸኮ ዞን የጉራፈርዳ ወረዳ ነዋሪዎች ናቸው።
ነዋሪዎቹ በወረዳው ባለፉት አመታት ተከስቶ በነበረው የፀጥታ ችግር ሳቢያ በአካባቢው ልማትና ዕድገት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጥሮ እንደነበር ተናግረዋል
አሁን ላይ በወረዳው አንፃራዊ ሠላም በመገኘቱ የአካባቢው ማህበረሰብ ወደ ልማት መግባት መቻሉን ነው የተናገሩት።
በወረዳው የተገኘውን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል የበኩላቸውን ሚና እንደሚወጡም ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።
የጉራፈርዳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ስንታየሁ ከርካ ከዚህ ቀደም በወረዳው በነበረው የፀጥታ ችግር ለበርካቶች ሞት መፈናቀል የንብረት ውድመት ምክንያት ሆኖ እንደነበር ጠቁመዋል።
የወረዳውን ሰላምና ልማት ዳግም ለመመለስ አመራሩ በየደረጃው ከሚገኙ የፀጥታ አካላትና የሀይማኖት መሪዎች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ጋር በመቀናጀት ሰፊ ስራ መስራቱን ነው የተናገሩት፡፡
በአሁኑ ወቅት ወረዳው ወደ ቀደመ ሰላሙ በመመለሱ ያሉ አልሚ ባለሀብቶችን ጨምሮ ማህበረሰቡ ወደ ልማት ስራ እንዲገቡ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
የቤንች ሸኮ ዞን ሠላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ኮጁ ባዳካች በበኩላቸው በዞኑ ባለፉት አመታት በተለያዩ ወረዳዎች የተለያዩ አጀንዳዎችን መነሻ በማድረግ ፀረ ሠላም ሀይሎች የሠላም ዕጦት እንዲፈጠር ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
በዞኑ የተገኘውን አንጻራዊ ሰላም ዘላቂ ለማድረግ በየደረጃው ከሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል
ዘጋቢ፡ ጦያር ይማም – ከሚዛን ጣቢያችን
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለማየሁ ባውዲ በክልሉ የሚገኙ የየተለያዩ ብሔሮች ዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ !!
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አት ደመቀ መኮንን በመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ንግግር አደረጉ
300 ለሚሆኑ ወላጅ አጥ ተማሪዎች ኢትዮ- ቴሌኮም ሳውላ ድስትሪክት ከ270 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ