የባህል እሴቶችን እና ሀገር በቀል እውቀቶችን በስፋት ማስተዋወቅ እንደሚገባ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ አስታወቀ ።
በዚህ ዙርያ በከልሉ ለማገኙት ሙያተኞች ና ለባለ ድርሻ አካላት ስልጠና ተሰጥቷል ።
በስልጠናው ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የክልሉ ባህል ፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፈንታሁ ብላቴ የብሄር ብሄረሰቦች ና ህዝቦች ቱባ ባህላዊ ዕሴቶች ሀገር በቀል ዕውቀቶች ና የባህል ተምሳሌቶችን በተደራጀ መልኩ ለማስታወቅ ሚቹ መድረክ ለመፈጠር የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን አብራርተዋል ።
በዘርፉ ለተሰማሩት ባለሀብቶች ፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ፤ ሙያ ማህበራት ኢንተርፕራይዞች ፣ ወጣቶችና ሴቶች ለልምድ ልውውጥ የስራ ዕድልና የገበያ ትስስር ለመፈጠር እንደሚረዳም አክለዋል ።
የቢሮ ምክትል ኃላፊ ና የባህልና ቱሪዝም ዘርፍ ኃላፊ አቶ አክሊሉ ለማ በበኩላቸው የባህል ፌስቲቫል፣ ካርኒቫልና ኤግዚብሽን መካሄድ የክልሉን ብሄሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች በተፈጥሮ የታደሉትን በታሪክ ያካበቱትን ቱባ ባህል ፣ እሴቶች ቋሚና ተንቀሳቃሽ ቅርሶችን የኪነ-ጥበብና የዕደ-ጥበብ ትውፊቶችን ለማስተዋወቅ ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል ።
ወጣቱ ትውልድ የባህልን ልማታዊ አስተዋጽኦ ግንዛቤ ለመፈጠር በማንነቱ የሚኮራ ትዉልድ ለመፈጠር ጉልህ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።
ፌስቲቫል፣ካርኒቫል ና ኤግዚብሽን ስናካሂድ ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶችና አሉታዊ መጤ ባህሎችን ደረጃ በደረጃ በመቀነስ ብሎም በማስቀረት መሆን እንዳለበት ምክትል የቢሮ ኃላፊ አጽንኦት ሰጥተዋል ።
ስልጠናው በክልሉ ላሉት ከስድቱም ዞኖች ለተወጣጡ ለባህል ሙያተኞች ና ለባድርሻ አካላት የተሰጠ ሲሆን ከእነሱም መካከል አንዳንዶቹ በሰጡበት አስተያየት በየአካባቢያችን ፌስቲቫል፣ካርኒቫልና ኤግዚብሽን እጅግ የሚጠቅም ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል
More Stories
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለማየሁ ባውዲ በክልሉ የሚገኙ የየተለያዩ ብሔሮች ዘመን መለወጫ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ !!
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አት ደመቀ መኮንን በመንግስታቱ ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ንግግር አደረጉ
300 ለሚሆኑ ወላጅ አጥ ተማሪዎች ኢትዮ- ቴሌኮም ሳውላ ድስትሪክት ከ270 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ