የማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ሲሳይ አስማረ እንደገለጹት÷ የዘርፉ ዳግም መነቃቃት ለላኪዎች ጥሩ አጋጣሚ ፈጥሯል።
የግብርና ምርቶችን እሴት ጨምረው የሚልኩ ኢንዱስትሪዎች ለውጭ ምንዛሬ ግኝት አስተዋጽኦ እያደረጉ
መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ማኅበሩ 230 ሺህ ሜትሪክ ቶን ሰሊጥ ወደ ውጪ ለመላክ መዘጋጀቱን ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡
ለአርሶ አደሮች ከማሳ ጀምሮ አጠቃላይ የምርት ሂደት ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በዱባይ ዓለም አቀፍ የቅባት እህሎች ኮንፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ሬንዲ ዳኩሬት ኢትዮጵያ ለግብርናው ዘርፍ በሰጠችው ልዩ ትኩረት ጥራት ያላቸው ምርቶች ለዓለም ገበያ እየቀረቡ ነው ብለዋል፡፡
More Stories
የዘንድሮው በዓል የቁም እንስሳት ግብይት መጠነኛ የዋጋ ጭማሪ የታየበት ነው ሲሉ በቤንች ሸኮ ዞን በዋቻ ገበያ የተገኙ ሸማቾች ተናገሩ
የኑሮ ውድነት ለመቋቋም በአጭር ጊዜ የሚደርሱ የጓሮ አትክልቶችን እያለማን ነው – በጌዴኦ ዞን የይርጋጨፌ ወረዳ ሞዴል አርሶአደሮች
የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን በማዘመንና የውስጥ የገቢ አቅሞችን ለይቶ በመሰብሰብ ለአካባቢዉን ልማት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው – የሺሺንዳ ከተማ አስተዳደር የኢኮኖሚ ክላስተር ጽ/ቤት