
የአፍሪካ ኩራት
ሳዲዮ ማኔ በዜግነት ሴኔጋላዊ ሲሆን የተወለደው 1992 እ.ኤ.አ ከሴኔጋል ዋና ከተማ 500 ማይል በምትርቀው ሴዲሆ ከተማ ነው። ቤተሰቦቹ በጣም ደሀ ስለነበሩ ከአጎቱ ጋር መኖር ጀመረ፤ የኳስ ፍቅሩ በልጅነቱ የተቀረፀው ማኔ እግር ኳስን በጎዳና ላይ በመጫወት እግሮቹን አፍታታ፡፡ ወላጆቹ ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄድ አለመገፋፋታቸዉ ሙሉ ትኩረቱን እግር ኳስ ላይ እንዲያደርግ አስቻለው። እግር ኳስ ብቃት ያላቸውን ለመመልመል ብዙ ታዳጊዎች ተሰልፈዋል፡፡ ሳዲዮም ተራ እስኪ ደርሰው ሰልፍ ይዟል፡፡ ነገር ግን የመልማዩ ዓይን 500 ማይል ከተጓዘው የ15 አመቱ ታዳጊ ላይ አረፈ፡፡ ወደ እሱም ተጠግቶ “በዚህ ጫማ እና ቁምጣ ነው የምትጫወተው?” አለው፡፡
አምስቱ ሙሽሮች
አፍሪካ በዓለም ዋንጫ መድረኮች 5 ቡድኖችን የማሳተፍ ዕድል አላት፡፡ ኮታዋ በ5 ቡድኖች ብቻ መወሰኑ አሁን ድረስ አነጋጋሪ ቢሆንም ፊፋ ለዚህ ጉዳይ ጆሮ አልሰጠም። 54 በፊፋ እውቅና ያገኙ ሀገራትን አቅፋ የያዘችው አህጉሪቱ፣ እነዚሁን ሀገራት በምድብ በመደልደል ማጣሪያ ካደረገች በኋላ ወደ መድረኩ ትልካለች፡፡
“ባሎንዶር” በሻርሌ ቲያትር አዳራሽ
በዓለም ዙሪያ በቢሊየን የሚቆጠሩ ተመልካቾችና ወዳጆች እንዳሉት የሚነገርለት እግር ኳስ፣ በቡድን ውጤታማ የሚኮንበት ስፖርት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ለተወዳጅነቱ ግለሰቦች ወይም ደግሞ ተጫዋቾች ምክንያት እንደሆኑ ምስክር አያስፈልግም፡፡ ምስክር ካስፈለገ ግን ኤድሰን አራንቴስ ዶ ናሲሜንቶ ፔሌ፣ ዲዬጎ አርማንዶ ማራዶና፣ ዮሃን ክራይፍ፣ አልፍሬዶ ዲስቴፋኖ፣ ጋሪንቻ፣ ፈረንክ ፑሽካሽ፣ ፍራንዝ ቤክንባወር፣ ሮናልዶ ልዊስ ናዛርዮ ዴሊማ፣ ሮናልዲንሆ የ2022 የኳታሩ ዓለም ዋንጫም ከዚህ የተለየ አዲስ አሰራር አልተከተለም፡፡