
በስምንት ዘመናዊ ስቴዲየሞች 32 ሃገራት የሚፋለሙበትና ታላላቅ የእግር ኳስ ጠቢባን የሚተውኑበት የዘንድሮው የአለም ዋንጫ ከወዲሁ የበርካታ መገናኛ ብዙሃንን ቀልብ እየገዛ ይገኛል።
አመሻሽ 11:00 ሰዓት ላይ የመክፈቻ ፕሮግራም የሚካሔድ ሲሆን ከኳታር ርዕሰ-መዲና ዶሃ በ51 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘውና በድንኳን ቅርፅ የተሰራው 60 ሽህ ተመልካቾችን የሚይዘው አል በይት ስቴዲየም የዘንድሮው የአለም ዋንጫ ጅማሮ ማብሰሪያ ይሆናል።
በአለም አቀፉ እግር ኳስ የበላይ ጠባቂ (FIFA) ጥሩ ሳውንድ-ትራክ ተብሎ የተመረጠውና አብሮነት ይሻላል የተሰኘው ሙዚቃ በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ታላላቅ የስፖርቱ ዓለም ሰዎች በተገኙበት የሚቀርብ ይሆናል።
የጌዴኦ ዲላ ስፖርት ክለብ ህዝባዊነቱን ለማረጋገጥ ህዝቡ በባለቤትነት ተሳታፊ እንዲሆን መስራት እንደሚገባ ተጠቆመ
ሀዋሳ፡ ሕዳር 09/2015 ዓ.ም (ደሬቴድ) ክለቡን ለማጠናከር ህዝቡ በባለቤትነት ተሳታፊ እንዲሆን ለማድረግ መሥራት ይጠበቅብናል ሲሉ የጌዴኦ ዲላ ስፖርት ክለብ ሰብሳቢ ተናግረዋል።
የጌዴኦ ዲላ ስፖርት ክለብ የ2015 የወንዶች እና የሴቶች ተጫዋቾች የሽኝት ሥነ-ሥርዓት በጌዴኦ ዞን ወጣቶች እና ስፖርት መምሪያ አዘጋጅነት ተካሂዷል።
በሽኝቱ ወቅት የተገኙት የጌዴኦ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ እና የጌዴኦ ዲላ ስፖርት ክለብ የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ዝናቡ ወልዴ እንደተናገሩት፥ ባደጉ ሀገራት ስፖርት ራሱን የቻለ የቱሪስት መስህብ እና ትልቅ ዋጋ የሚከፈልበት ሲሆን ባላደጉት ሃገራት ዘርፉ ኋላ ቀር እና በመንግስት ጫንቃ ብቻ የተንጠለጠለ በመሆኑ ከዘርፉ የሚፈለገው ውጤት አልተገኘም።
“እግር ኳስ የሞተበት ዕለት”
በአንዱዓለም ሰለሞን
“ፈጽሞ ከዚህ ምድር የመጡ አይመስሉም ነበር፡፡ ያ የብራዚል ቡድን ስብስብ ካየኋቸው ሁሉ ምርጡ ነው፡፡ እነዛ ተጫዋቾች ዐይኖቻቸው በጨርቅ ቢሸፈኑ እንኳ ማን የት ቦታ እንዳለ የሚያውቁና እርስ በእርስ የሚተዋወቁ ይመስሉ ነበር፡፡”
ይህ አባባል በአንድ ወቅት ጣሊያናዊው የፊት መስመር ተጫዋች፣ ፓውሎ ሮሲ ስለ 1982ቱ የብራዚል ብሄራዊ ቡድን ተጫዋቾች የተናገረው ነው፡፡
ብራዚል በሁሉም የዓለም ዋንጫ ውድድሮች የተካፈለች ብቸኛዋ ሀገር ናት፡፡ የዓለም ዋንጫውን አምስት ጊዜ በማሸነፍም በቀዳሚነት ትጠቀሳለች፡፡ እ.ኤ.አ በ1950 እና 2014 ውድድሩን ብታስተናግድም ዋንጫውን ግን ማስቀረት አልቻለችም፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ ባዘጋጀችው ውድድር ለፍጻሜ የደረሰች ቢሆንም በታላቁ ማራካና ስታዲየም በዑራጓይ 2ለ1 ተሸንፋ ዋንጫውን ተነጥቃለች፡፡ ይህም ለእግር ኳስ የተለየ ፍቅር ያለውን የብራዚል ደጋፊ ልብ በሀዘን የሰበረ ብቻም ሳይሆን የተወሰኑ ደጋፊዎችን ህይወት የቀጠፈ ጭምር ሆኖ አልፏል፡፡
በ2014 ባዘጋጀችው ውድድር በግማሽ ፍጻሜው በጀርመን የደረሰባት ያልተጠበቀ የ 7ለ1 ሽንፈትም እንዲሁ የደጋፊዎቿን አንገት አስደፍቷል፡፡
በ1982 በስፔን በተካሄደው የዓለም ዋንጫ የተካፈለው የብራዚል ብሔራዊ ቡድን በመሰል ታሪክ፣ ግን ደግሞ በተለየ መልኩ በስፖርቱ አፍቃሪዎች ዘንድ ይታወሳል፡፡
“ዋንጫውን አላነሳንም፡፡ ሌላው ቀርቶ ለግማሽ ፍጻሜ እንኳ አልደረስንም፡፡ ነገር ግን መላው ዓለም የ 1982ቱን የብራዚል ብሄራዊ ቡድን ያስታውሰዋል፡፡ ይህ መሆኑም ያስደስተኛል” በማለት በወቅቱ የቡድኑ ተጫዋች የነበረው ኤደር በአንድ ወቅት ባደረገው ቃለ መጠይቅ ተናግሯል፡፡
በስፔኑ የዓለም ዋንጫ ቢጫ ለባሾቹ በመጀመሪያው ዙር ማጣሪያ ከቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት፣ ስኮትላንድ እና ኒውዝላንድ ጋር ነበር የተመደቡት፡፡ በመጀመሪያው ጨዋታ ከሶቭየት ህብረት ጋር ተገናኙ፡፡
“የመጀመሪያ ጨዋታ ምንጊዜም ከባድ ነው፡፡ ሌሊቱን እንቅልፍ ሳይወስደኝ ነበር ያደረው” በማለት ኤደር ስለ ሁኔው ያስታውሳል፡፡
ሶቭየቶች ቀድመው ጎል አስቆጠሩ። ቀጥሎ አምበሉ ሶቅራጥስ የአቻነቷን ጎል ለብራዚሎች አገባ፡፡ በመጨረሻም ባለቀ ሰዓት የተቆጠረችው የኤደር ሁለተኛ ጎል ብራዚልን ሙሉ ነጥብ እንድታገኝ አደረጋት፡፡
በቀጣይ ስኮትላንድን ገጠሙ፡፡ ስኮትላንዶች ጨዋታው በተጀመረ በ 17ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠሩት ጎል መምራት ጀመሩ። ለእረፍት ከመውጣታቸው አስቀድሞ፣ በ 33ኛው ደቂቃ ላይ ዚኮ ብራዚልን አቻ አደረገ። ከእረፍት መልስ ቢጫ ለባሾቹ ፍጹም ልዩ ነበሩ፡፡ ኦስካር፣ ኤደርና ፋልካኦ ከመረብ ባሳረፏቸው ጎሎች ብራዚል 4ለ1 አሸነፈች፡፡
ከኒውዝላንድ ጋር በነበረው ጨዋታ የቢጫ ለባሾቹ ኮከቦች ሜዳው ላይ እንደልባቸው ፈነጩበት፡፡ ከእረፍት በፊት ዚኮ ባስቆጠራቸው ሁለት ጎሎች እየመሩ እረፍት ወጡ፡፡ ከእረፍት መልስ ፋልካኦና ሰርጂንሆ ሁለት ጎሎችን አክለው አራት ለባዶ አሸነፉ፡፡
በወቅቱ በነበረው የፊፋ ህግ መሰረት ለሩብ ፍጻሜ የሚያልፉ ቡድኖች በሚታወቁበት የሁለተኛው ዙር የምድብ ጨዋታ ከጣሊያንና አርጀንቲና ጋር ተመደቡ፡፡ የመጀመሪያውን ጨዋታ ያደረጉት የምንጊዜም ተቀናቃኛቸው ከሆኑትና በ 1978 ዋንጫውን ከወሰዱት አርጀንቲና ጋር ነበር፡፡
“ሁለታችንም በሚገባ እንተዋወቃለን፡፡ ይህ ወሳኝ ግጥሚያ ነበር” በማለት ሰርጂንሆ ስለጨዋታውና በወቅቱ ስለነበረው ስሜት ይናገራል፡፡
ብራዚላዊው አጥቂ “ወሳኝ” ባለው ግጥሚያ ለሀገሩ አንድ ጐል ከመረብ አሳረፈ፡፡ ጁንዬር እና ጊኮ ሁለት ጐሎችን አስቆጥረው በአጠቃላይ ብራዚሎች 3ለ1 በሆነ ውጤት የቀድሞ ሻምፒዮናዎቹን አንበረከኩ፡፡
ቀጣይ ተጋጣሚያቸው አርጀንቲናን 2ለ1 ያሸነፈችው ጣሊያን ነበረች፡፡ ምንም እንኳ “አዙሪዎቹ” አርጀንቲናን ቢያሸንፉም፣ በመጀመሪያው ዙር የምድብ ማጣሪያ በሶስቱም ጨዋታዎች አቻ በመውጣት ነበር ከምድባቸው ያለፉት፤ ከፖላንድ ጋር 0ለ0፣ ከፔሩና ካሜሩን ጋር 1ለ1 በመለያየት፡፡ ይህ ደግሞ ቢጫ ለባሾቹ ጣሊያንን በእርግጠኝነት እንደሚያሸንፉ እንዲሰማቸው አደረጋቸው፡፡ ከዚህ ባሻገር ብራዚሎች ወደ ቀጣዩ ዙር ለማለፍ አቻ መውጣት የሚበቃቸው መሆኑ በራስ መተማመናቸውን የበለጠ ከፍ አደረገው፡፡
ያም ሆኖ በባርሴሎና ሳሪና ስታዲየም የተደረገው የሁለቱ ሀገራት ጨዋታ የብዙዎችን ግምት የሚያፈርስ፣ በብራዚሎች ብቻም ሳይሆን በመላው ዓለም የእግር ኳስ አፍቃሪ ዘንድ ሁሌም የሚታወስ ሆነ፡፡
የውድድሩ ክስተት የነበረው የጁቬንቱሱ ኮከብ፣ ፓውሎ ሮሲ ባስቆጠራቸው ሶስት ጎሎች የእግር ኳስ ጠበብቶቹ ጉዞ ተገታ፡፡ ሶቅራጥስ እና ፋልካኦ ለቢጫ ለባሾቹ ሁለት ጎሎችን ከመረብ ቢያሳርፉም ብራዚል 3ለ2 በሆነ ውጤት ተሸንፋ ከውድድሩ ውጪ ሆነች፡፡
“በሳሪያ ስታዲየም በገጠመን ነገር ሁላችንም አዝነን ነበር፡፡ ምክንያቱም ይህ ጥሩ ስሜት የሚፈጥር ነገር አልነበረም። ከጨዋታው በኋላ ስብሰባ ነበረን፡፡ ነገር ግን ማንም ምንም ለማለት አልቻለም። በወቅቱ ሁኔታውን ለመግለጽ ለማናችንም ከባድ ነበር” በማለት ኤደር ሁኔታውን ያስታውሳል፡፡
የብዙዎችን ቀልብ የገዛው የብራዚሎች አጨዋወት ልክ መድረክ ላይ እንደሚታይ አስደሳች ትዕይንት ነበር፡፡ ኳስን በማራኪ ሁኔታ መቀባበል፣ በፍጥነት ወደ ፊት መሮጥና የተቃራኒ ቡድን ተጫዋቾችን ማስጨነቅ ለእነሱ ቀላል ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ በተከላካይ ስፍራ ላይ የሚጫወቱ ተጫዋቾቻቸው ሳይቀር የአጥቂነት ሚና የነበራቸው መሆኑ ጠቅሟቸዋል፡፡
“የጨዋታ ፍልስፍናችንን ሳንቀይር ነበር የተጫወትነው፡፡ የዓለም ዋንጫውን ማሸነፍ እንፈልግ ነበር፡፡ ግን ደግሞ ተሸነፍን፡፡ ይመስለኛል ያ ስብስብ እግር ኳስን ከዚህ በተለየ መንገድ መጫወትን አያውቅም” በማለት ለሽንፈት የተዳረጉበት ምክንያት በወቅቱ እንደሁኔታው የተለየ የአጨዋወት ስልት ባለመከተላቸው እንደነበር ዚኮ ይገልጻል፡፡
ሉዚንሆ በበኩሉ፡-
“ጨዋታው ሁለት አቻ ሳለ እኔና ኦስካር ተከላካዮቹ በቦታቸው ሆነው እንዲከላከሉ ለመንገር ስንጮህ ነበር፡፡ አሰልጣኛችን ግን ውጤቱን ማስጠበቅ ሳይሆን ጨዋታውን ማሸነፍ ነበር የሚፈልገው” ብሏል፡፡
እርግጥ ነው፤ የቴሌ ሳንታና ፍልስፍና “የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው” የሚል ዓይነት አልነበረም፡፡ ከማሸነፍ ባሻገር ብራዚሎች የሚታወቁበትን ማራኪ ጨዋታ ማሳየት ይፈልጋል፡፡ ዚኮ ስለጉዳዩ በሰጠው አስተያየትም ይህንኑ እውነታ ይነግረናል፡-
“ከጣሊያን ጋር ከመጫወታችን አስቀድሞ በመልበሻ ክፍል ውስጥ ሳለን ቴሌ አቻ መውጣት ለግማሽ ፍጻሜ እንደሚያሳልፈን ጠቁሞን፣ በዚህ ዘና እንዳንል ግን ነግሮን ነበር፡፡ እሱ በፍጹም ወደ ኋላ እንድንል (እንድንከላከል) አልነገረንም፤ ትኩረታችን ሁልጊዜም ለማሸነፍ መሆን እንዳለበት እንጂ። ይህ ደግሞ እውነተኛው የብራዚላዊያን የአጨዋወት ዘይቤ ነው”
አሰልጣኛኙ በተከተለው አጨዋወት በብዙዎች ተወድሷል፡፡ ስለዚህ ጉዳይ ኤደር ምስክርነቱን ሲሰጥ፡-
“ከጣሊያን ጋር ካደረግነው ጨዋታ በኋላ የነበረውን ሁኔታ አስታውሳለሁ፡፡ ቴሌ መግለጫ የሰጠው ከ300 በላይ ጋዜጠኞች ፊት ቆሞ ነበር፡፡ ሁሉም ግን አድናቆታቸውን ገልጸውለታል” በማለት ተናግሯል፡፡
ፋልካኦ በበኩሉ፡-
“ብራዚል በ1982ቱ የዓለም ዋንጫ ከጣሊያን ጋር ባደረገችው ጨዋታ ተሸንፋለች፤ ነገር ግን በታሪክ ታላቅ ስም አግኝታለች” በማለት ቡድኑ በስፖርት አፍቃሪው ዘንድ ያሳደረውን ተጽዕኖና የተቸረውን ከበሬታ ያስታውሳል፡፡
ተጫዋቾቹ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ደማቅ አቀባባል ነበር የተደረገላቸው፡፡ ያም ሆኖ አብዛኞቹ የቡድኑ አባላት ሽንፈታቸውን አምኖ ለመቀበልና ከሀዘናቸው ለማገገም ረጅም ጊዜ ወስዶባቸዋል፡፡ ለዚህም ይመስላል ይህ ስሜት ከተሰማቸው ተጫዋቾች አንዱ የሆነው ሶቅራጥስ የዛን ቀኑን ክስተት “እግር ኳስ የሞተበት ዕለት” በማለት የገለጸው፡፡


የአፍሪካ ኩራት
ሳዲዮ ማኔ በዜግነት ሴኔጋላዊ ሲሆን የተወለደው 1992 እ.ኤ.አ ከሴኔጋል ዋና ከተማ 500 ማይል በምትርቀው ሴዲሆ ከተማ ነው። ቤተሰቦቹ በጣም ደሀ ስለነበሩ ከአጎቱ ጋር መኖር ጀመረ፤ የኳስ ፍቅሩ በልጅነቱ የተቀረፀው ማኔ እግር ኳስን በጎዳና ላይ በመጫወት እግሮቹን አፍታታ፡፡ ወላጆቹ ወደ ትምህርት ቤት እንዲሄድ አለመገፋፋታቸዉ ሙሉ ትኩረቱን እግር ኳስ ላይ እንዲያደርግ አስቻለው። እግር ኳስ ብቃት ያላቸውን ለመመልመል ብዙ ታዳጊዎች ተሰልፈዋል፡፡ ሳዲዮም ተራ እስኪ ደርሰው ሰልፍ ይዟል፡፡ ነገር ግን የመልማዩ ዓይን 500 ማይል ከተጓዘው የ15 አመቱ ታዳጊ ላይ አረፈ፡፡ ወደ እሱም ተጠግቶ “በዚህ ጫማ እና ቁምጣ ነው የምትጫወተው?” አለው፡፡