- ዜናዎች
- Wednesday, 25 September 2019
- ashenafi
የምስራቅ አፍሪካ አገራት አመራሮች ለፈጠሩት ሰላምና የኢኮኖሚ ትስስር እውቅና ተቸራቸው
የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ፣ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂና የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሙሃመድ አብዱላሂ የኮንኮርዲያ ዓመታዊ የአመራር ሽልማት አሸናፊ ሆነው ተመረጡ።
መሪዎቹ ሽልማቱን አሸናፊ የሆኑት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ባሉ አገሮች መካከል ለተፈጠረው ሰላም እና የኢኮኖሚ ትስስር ላበረከቱት አስተዋጽፆ ነው።
ሶስቱ አመራሮች ተቀራርበውና ተደጋግፈው መስራት በመቻላቸው በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን እንዲሁም የኢኮኖሚ ትስስር እንዲፈጠር በማድረጋቸው የኮንኮርዲያ ዓመታዊ የአመራር ሽልማት አሸናፊ ለመሆን እንዳበቃቸው ሽልማቱን ያዘጋጀው ድርጅት ገልጿል።
ሽልማቱን በተባበሩት መንግስታት ስብሰበባ ላይ እየተካፈሉ የሚገኙት የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሙሃመድ አብዱላሂ ተቀብለዋል። ፕሬዚዳንቱ በሽልማቱን በተቀበሉበት ወቅት የቀጠናውን ሰላም ቀጣይነት ለማረጋገጥ የበለጠ እንደሚሰሩ ገልጸዋል ሲል ድርጅቱ በድረገጹ አስፍሯል።
- ዜናዎች
- Wednesday, 25 September 2019
- ashenafi
ኢትዮጵያ በመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ላስመዘገበችው ውጤት የዕውቅና ሽልማት አገኘች
ሀዋሳ፡ መስከረም 14/2012 ዓ.ም (ደሬቴድ) ኢትዮጵያ በመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ላስመዘገበችው ውጤት የዕውቅና ሽልማት ማግኘቷን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በኒውዮርክ ከተማ እየተካሄደ ባለው የተባበሩት መንግስታት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ላስመዘገበችው ውጤት የዕውቅና ሽልማት ለፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ተበርክቶላቸዋል::
ዉጤቱ ሊዘገብ የቻለው የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ የጀርባ አጥንት ሆነው በሚሰሩት የጤና ኤክስቴንሽን ሰራተኞች ትጋት እንደሆነ የጤና ሚኒስቴር ገልጿል::
ይህንን የዕውቅና ሽልማት ያበረከተው አክሰስ ቻሌንጅ በመባል የሚታወቅ መቀመጫውን አሜሪካን ሀገር ያደረገ በጤና እና ትምህርት ተደራሽነት ላይ የሚሰራ ድርጅት መሆኑ ተጠቁሟል::
ሽልማቱን ዶክተር ጽዮን ፍሬው ኢትዮጵያን በመወከል ተቀብላለች::
ምንጭ፡ የጤና ሚኒስቴር
- ዜናዎች
- Tuesday, 24 September 2019
- Isaac
“የግብጽ አዲስ ሀሳብ የድርድር ጭብጥ የለውም’’ - ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ
ሀዋሳ፡ መስከረም 13/2012 ዓ.ም (ደሬቴድ) “ግብጽ በድርድር ስም በቅርቡ ያቀረበችው ‹አዲስ ሀሳብ› የድርድር ጭብጥ የለውም” ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል ፕሮፌሰርና የውሃ ፖለቲካ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ አስታወቁ። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ ለልማት ማዋልን ዋና ጉዳይ አድርጎ መስራቱም መዘንጋት እንደሌለበት ገለጹ።
- ዜናዎች
- Wednesday, 25 September 2019
- ashenafi
ሰባት ሚሊየን ብር የሚያወጣ ወርቅና በርካታ የዉጪ አገር ገንዘቦች ተያዙ
ሀዋሳ፡ መስከረም 14/2012 ዓ.ም (ደሬቴድ) በጉምሩክ ኮሚሽንየ ጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የቶጎ ጫሌ መቅርጫ ጣቢያ 7 ሚሊየን ብር የሚያወጣ 5 ኪሎ ግራም ወርቅና የውጪ አገር ገኝዘቦችን መያዛቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
መስከረም 13 ቀን 2012 ዓ.ም ከለሊቱ 9 ሰዓት አካባቢ ከሰሌዳ ቁጥር ኮድ3-05861 ድሬ አይሱዚ ኤክስፖርት የሚደረግ ጫት የጫነ ተሽከርካሪ የቶጎጫሌ ፈታሾች ባደረጉት ጥረትና ጠንካራ ፍተሻ 5 ኪሎ ግራም ጥፍጥፍ ወርቅ፤ 175 ሺህ 584 የሳውዲ ሪያል፣ 7 ሺህ155 ድርሀም 63 ሺህ 035 የአሜሪካን ዶላር እና 146 ሺህ 500 የሳውዲ ሪያል በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የቶጎ ጫሌ መቅረጫ ጣቢያ ፈታሾች ቀን ከሌሊት ህገ ወጥ የገንዘብ ዝዉዉርና ኮንትሮባንድን ለመከላከል እያደረጉት ላለዉ ጠንካራ ስራ የገቢዎች ሚኒስቴር ያለዉን አድናቆት ገለልጿል፡፡
የተያዘዉ ወርቅና ገንዘብ እንደተለመደዉ ለብሄራዊ ባንክ ገቢ ይሆናልም ተብሏል፡፡
ምንጭ፡ የገቢዎች ሚኒስቴር
- ዜናዎች
- Tuesday, 24 September 2019
- Isaac

ክልሎች በጥናት ላይ ያልተመሰረተ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ጀምረዋል