ትንቅንቅ
በፈረኦን ደበበ
ሰሞኑን ይሰማ የነበረው ከወትሮ ለየት ይላል፡፡ ውጥረት በበዛበት ዓለም የተለመደ ነው ከሚባለው ደረጃም በልጦ ተገኝቷል። በዓለም ህዝብ የሠላም ተስፋ ላይም ጥላ አጥልቶበታል፡፡
አዎን ጉዳዩ “የነብርን ጭራ ከያዙ ወደ ኋላ አይመለሱ” እንደሚባለው ነው፡፡ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ግለቱ ሲቀጥል ከግጭቱ ጋር ተያያዥ ነን ብለው እራሳቸውን የሚገልጹ አካላትም ወደ ፊት ለፊት እየወጡ ይገኛሉ። ለጦርነቱ ድጋፍ ላድርግ እንጂ በቀጥታ አልተሳተፍኩም የሚሉ ወገኖች ማንነትንም አጋልጧል፡፡
ቡድን 7 የተባለው የሀገራት ትብብር ደግሞ የሰሞንኛው ትርዒት አቅራቢ ሆነ። ከ2ተኛው ዓለም ጦርነት በኋላ ተመሥርቷል የተባለው ህብረት በኢንዱስትሪ የበለጸጉና የዳበረ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አራማጅ የሚባሉ ሀገራትን አቅፏል፡፡ በዚህ መጠሪያ ዓለምን እያሽከረክሩ ሲቆዩ ከአመለካከታቸው ወጣ የሚሉትንም እየለየ ዱላውን ሲያሳርፉ መጥተዋል፡፡