በወላይታ ሶዶ ከተማ የህዝብ የውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው
የውይይት መድረኩ የብልጽግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚና የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ዋና ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ፡ የክልሉ ገቢዎች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ዘይቱና ኢብራሂም፡ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አክሊሉ ለማ እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ነው የውይይት መድረኩ በመካሄድ ላይ የሚገኘው፡፡
በሶዶ ከተማ ከንቲባና በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ለውይይቱ የሚሆን የመነሻ ሀሳብ የቀረበ ሲሆን የውይይቱ ተሳታፊዎችም የተለያዩ ሀሳቦችን እያነሱ ይገኛሉ ።
ባለፉት ሁለት አመታት የክልሉን ህዝብ የመሰረተ ልማት ፍላጎት በማሳካት ረገድ አመርቂ ውጤት ማምጣት ተችሏል- የሲዳማ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ደሰታ ሌዳሞ
ሀዋሳ፡ ሰኔ 27/2014 ዓ.ም (ደሬቴድ) ባለፉት ሁለት አመታት ውስጥ የክልሉን ህዝብ የመሰረተ ልማት ፍላጎት በማሳካት ረገድ አመርቂ ውጤት ማምጣት መቻሉን የሲዳማ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ደሰታ ሌዳሞ ገልጹ።
የሲዳማ ብሄራዊ ከልላዊ መንግስት ሁለተኛ አመት ምስረታ በአሉን በሀዋሳ ከተማ ሲዳማ ባህል አዳራሽ እያከበረ ይገኛል።
የዘንድሮው የክረምት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን ዕምድብር ከተማ አስተዳደር ተጀምሯል
ሀዋሳ፡ ሰኔ 27/2014 ዓ.ም (ደሬቴድ) የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት የክልሉና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እየተካሄደ ነው።
በዚህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በሺዎች የሚቆጠሩ የክልሉ ወጣቶች እንደሚሳተፉ የሚጠበቅ ሲሆን በአረጋውያን ቤት እድሳት፣በደም ልገሳ፣ አረንጓዴ አሻራ የማኖር ዘመቻን ጨምሮ በ 13 በተመረጡ ልዩ ልዩ ዘርፎች የበጎ ፈቃድ ተግባራት ይከናወናሉ።
Read more: የዘንድሮው የክረምት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን ዕምድብር ከተማ አስተዳደር ተጀምሯል